Data Loading...
Amphi Magazine 3 Flipbook PDF
newfile
121 Views
96 Downloads
FLIP PDF 1.08MB
በዩኒሽርሲቲ ተማሪዎች የምትዘጋጅ ዲጅታል መፅሔት
አምፊ የማትረባ ፍየል ዘጠኝ ትወልዳለች እነሱም ያልቃሉ እሷም ትሞታለች
Jeequmsa /midhaan mana kessaa Nature-Inspired Algorithm
ቁጥር 3 ነሐሴ 2012
4 ዕድ
19 ፍልስምና
8
ፈታ ብዕር
22
ሚስማር ተራ
12
የኔታ
24
ጋሜ
15
25 አመልካች ጣት
ኪን
Vol. 3
ርዕሰ-መፅሔት
amPhi
መልዕክተ - አምፊ የአምፊ ወዳጆች
እንኳን ደስ አለን! ዳግማዊ አድዋ - ህዳሴ ግድብ። አድዋ ጥቁር በነጭ ላይ የበላይ የበላይነት የወሰደበት ሳይሆን በተባበረ ክንድ ነጻነት በጭቆና ላይ የበላይነት የወሰደበት ነው። ህዳሴም የዚህ አልገዛም ባይነት እና አርበኝነት ሌላ ክስተት ነው። የስኬት ፍጻሜውን በጉጉት እንጠብቃለን። በወጣቱ ድምጻዊ ሐጫሉ ሑንዴሳ እንዲሁም በሌሎች የወገኖቻችን ህልፈተህይወት የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን መግለጽ እንወዳለን። ለቤተሰቦቻቸው እና ለመላው ኢትዮጵያዊያን ልባዊ መጽናናትን እንመኛለን። እኛም ትኩረታችን በዩኒቨርሲቲዎች እንደመሆኑ ለተማሪዎች እና ለወጣቶች ሰላማዊ እና የሰከነ የልዩነት አፈታት መንገድን እንድናዳብር እንመክራለን። ልዩነቶችን በሰላማዊ መንገድ ከመፍታት ወጪ ብዙ ርቀት የሚወስድ የተሻለ መንገድ የለንም። የኮቪድ ማዕበል ፍጥነቱን እየጨመረ ነው። ድንጋጤና እና ጥንቃቄው ደግሞ በተቃራነው እየቀነሰ ነው። በተቻለን መጠን የጥንቃቄ መመሪያዎችን ተግብረን ለሌሎች መያዝ ምክንያት ላለመሆን እንሞክር። ለአዲሱ ዓመት በሰላም ያድርሰን!!!
አዘጋጆች አዘጋጅ ተስፋ ብዙወርቅ ግራፊክስ ዲዛይን የማህበራዊ ሚዲያ ዘዋሪ ዮናስ ሞሐመድ ኤዲተሮች እየሩሳሌም መስፍን ታሪኩ ገላሼ በዚህ ያግኙን Email:[email protected] Telegram:- Amphi Instagram:- @amphimagazine Fb:- Amphi Magazine Twitter:-amphimagazine Mob:- 0935440749 , 0923507547
ነሐሴ 2012
Vol. 3
ዕድ
amPhi
Nature-Inspired Algorithm Eyob Mersha
Optimization problems, subject to complex nonlinear constraints, are the main problems in science and engineering. Since the traditional algorithms are inefficient to deal with such nonlinear problems, it requires a sophisticated optimization algorithm. As it is known that nature provides some of the efficient ways to solve its problems. To formulate these sophisticated algorithms, researchers look around their environment and propose different nature-inspired algorithms. A current trend is to use nature-inspired algorithms due to their flexibility and effectiveness. These nature driven algorithms have a variety of applications in our day today’s technology lead life. For instance, a swarm intelligence category algorithm is used to solve optimization problems in engineering and computer science fields. Nature has inspired many researchers in many ways and thus is a rich source of inspiration. The name ”nature-inspired algorithms” itself indicates that there are several algorithms that have been developed by mimicking the natural process or phenomena. Nowadays, most new algorithms are nature-inspired, because they have been developed by drawing inspiration from nature. In the most generic term, the main source of inspiration is Nature. Therefore, almost
4
ነሐሴ 2012
all new algorithms can be referred to as nature-inspired. By far the majority of nature-inspired algorithms are based on some successful characteristics of the biological system. Therefore, the largest fraction of nature-inspired algorithms are biology-inspired, or bio-inspired for short. Nature-inspired algorithms are a set of novel problem-solving methodologies and approaches and have been attracting considerable attention for their good performance. Representative examples of nature-inspired algorithms include swarm intelligence (SI) based algorithms such as particle swarm optimization(PSO), artificial neural networks (ANN), fuzzy systems (FS), evolutionary computing (EC), genetic algorithms(GA), ant colony optimization (ACO), water cycle algorithms (WCA), gravitational search algorithm (GSA) and, and they have been applied to solve many real-world problems. As their name depicts that these algorithms are derived from natural phenomena.
All SI-based algorithms use multi-agents, inspired by the collective behavior of social insects, like ants, termites, bees, and wasps, as well as from other animal societies like flocks of birds or school of fish. The classical particle swarm optimization (PSO) uses the swarming behavior of fish and birds, while the firefly algorithm (FA) uses the flashing behavior of swarming fireflies. Cuckoo search (CS) is based on the brooding parasitism of some cuckoo species, while bat algorithm uses the echolocation of foraging bats. Ant colony optimization uses the interaction of social insects (e.g., ants), while the class of bee algorithms are all based on the foraging behavior of honey bees. PSO which is developed by Eberhart and Kennedy in 1995, which was inspired by the social behavior of bird flocking and fish schooling. The inspiration comes from the observation of mass of birds flocking together without any collision. What makes them flock together smoothly? How each bird exchange information with their neighbor about velocity that makes stay them in the swarm, direction which allow to flow together in mass as one entity? A similar observation in fish schooling also inspires PSO. PSO utilizes a “population” of particles that...
Vol. 3
ዕድ
fly through the problem hyperspace with given velocities. At each iteration, the velocities of the individual particles are stochastically adjusted according to the historical best position for the particle itself and the neighborhood’s best position. Both the particle best and the neighborhood best is derived according to a user-defined fitness function. Particle Swarm Optimization can be considered as an evolutionary computation technique inspired by the social behavior of individuals in groups in nature. The behavior of any individual in the swarm is influenced by its own experience and that of its neighbors. The movement of each particle naturally evolves to an optimal or near-optimal solution. The word “swarm” comes from the irregular movements of the particles in the problem space, now more similar to a swarm of mosquitoes rather than a flock of birds or a school of fish. The main application of nature-inspired algorithms are antennas, biomedical, communication networks, clustering and classification, combinatorial optimization, control, design, distribution networks, electronics and electromagnetics, engines and motors, entertainment, diagnosis of faults, financial, fuzzy and neuro-fuzzy, graphics and visualization, image and video, metallurgy, modeling, neural networks, prediction and forecast-
5
ነሐሴ 2012
ing, power systems and plants, robotics, scheduling, security and military, sensor networks, signal processing. Not all metaheuristic algorithms are bio-inspired, because their sources of inspiration often come from physics and chemistry. For the algorithms that are not bio-inspired, most have been developed by mimicking certain physical and/ or chemical laws, including electrical charges, gravity, river systems, etc. One best example which can be categorized under this type of algorithm is the Water Cycle Algorithm (WCA). WCA is an algorithm inspired by the hydrological cycle of water. The water droplets from rain are considered as one fundamental entity or particle in this algorithm. This particle collected and form a pond, the ponds together run towards a nearby river, rivers find their journey toward their nearest sea. At last, the sea flows to their last destination, the ocean. Then by the evaporation process, the process repeats itself. This hydrological cycle was proposed as an algorithm and used in a variety of applications. One of its best application is in image enhancement. Even though it has not been studied scientifically, the Ethiopian Orthodox Church Calendar has an algorithm that fell into this Physics inspired algorithms. Because this calendar uses a solar calendar and lunar calendar. A solar calendar
amPhi
is a calendar whose dates indicate the position of the earth on its revolution around the sun. Whereas, a lunar calendar is one in which days are numbered within each lunar phase cycle. Though most of the public holidays fall on the same date from year to year, some of the religious holidays such as Ethiopian Good Friday, Easter, Ed Alfetir, Arefa, and Mewulid fall on different dates and months from year to year. To determine the date and month of those religious holidays, it requires calculations based on mathematical techniques or algorithms used by both religions. The calculation of the fasting dates is based on the book ‘’ አቡሻሀር ‘’ which was written by “ዲሚጥሮስ’’. Particularly how fasting dates are calculated is an inspiration of earth and moon revolution around sun and earth respectively.
*Eyob Mersha (MSc) lecturer of Haramaya Institute of Technology, School of Electrical and Computer Engineering.
Vol. 3
ዕድ
amPhi
ዲጂታል: ገንዘቦች ልዑልሠገድ ጥላሁን
በአንድ ሀገር ወይም ማህበረሰብ ውስጥ የተለያዩ ቁሳቁሶችን እና አገልግሎቶችን (Services) ለመሸመት የሚያገለግል ማንኛውም ነገር ሁሉ ገንዘብ ይባላል ።የመገበያያ ገንዝብ ባልነበረበት ጊዜ የጥንት ሰዎች ግብይት የሚያካሂዱት የሚተዋወቁ ሰዎች ከሆኑ በስጦታ ልውውጥ ሲሆን የማይተዋወቁ ሰዎች ከሆኑ ግን እቃን በእቃ በመለዋወጥ ነበር ። ይህ የግብይት ዘዴ ከ100,000 ዓመታት በፊት እንደተጀመረ ይነገራል። የተለያዩ የጋማ እና የቀንድ እንስሳትን ፣ ማርን ፣ ቅቤን ፣ ጥራጥሬዎችን እና የእህል አዝርዕት ምርቶችን ሰዎች ይለዋወጡ ነበር ፡፡ ገንዘብ የተፈጠረው ታሪክ መጻፍ ከመጀመሩ በፊት ስለሆነ የትኛውም ስለገንዘብ አጀማመር የሚተርክ ታሪክ በግምታዊ (conjecture) እና ምክንያታዊ ሆነው ከመረጃዎች ተነስተው በተወሰኑ ውሳኔዎች (logical inference) ላይ የተመሰረተ ነው ። በጥንት ታሪክ ውስብስብነት ማለትም የጥንት ስልጣኔዎች በተለያየ ፍጥነት ስላደጉ ፣ ትክክለኛ መዛግብትን ስላላሰቀመጡ ወይንም መዛግብቶቻቸው ስለወደሙ ፣ የጥንት ምጣኔ ሀብታዊ ስርአት (anicent economic system) ከታሪክ ጽህፈት ስለሚቀድም በእነዚህ እና መሰል ምክንያቶች የልውውጥ ስርአት በገንዘብ ስርአት የተተካበትን ጊዜም ሆነ የገንዘብ ፈጠራን ምንጭ ዱካ ማግኘት አልተቻለም ።
የገንዘብ ዝግመተ ለውጥ በዓለማችን የሚገኙ የተለያዩ ማህበረሰቦችና ባህሎች ቀስ በቀስ ኮሞዲቲ ገንዘብ (commodity money) መጠቀም ጀመሩ ። የኮሞዲቲ ገንዘብ ዋጋ የሚመነጨው እራሱ ገንዘቡ ከተሰራበት ቁስ ነው። እንደ ወርቅ ፣ ብር ፣ ነሃስ ፣ አተር ፣ ትልልቅ ድንጋዮች ፣ ያጌጡ ቀበቶዎች ፣ ዛጎል ፣ካናቢስ ፣ ሲጋራ ፣ ሐር ፣ ጨው ወዘተረፈ... ያሉ ኮሞዲቲዎች ለግብይት አገልግለዋል። በአሁኑ ምዕራባዊ ቱርክ ግዛት አካባቢ ይኖሩ የነበሩት ልድያውያን ደግሞ በ600 ዓ/ዓ ለመጀመርያ ጊዜ የወርቅ እና የብር ሳንቲሞችን ለዓለም እንዳስተዋወቁ ዝነኛው ግሪካዊው የታሪክ ጸሐፊ ሄሮዳተስ ዘግቧል ። በኢትዮጵያም በአክሱም ነገስታት ከ 270 ዓ/ም ጀምሮ የወርቅ እና የብር ሳንቲሞች ስራ ላይ ውለዋል ። በመካከለኛው ዘመን ደግሞ አሞሌ ጨው በጥንታዊው የኢትዮጵያ ንጉሳዊ ግዛት ዝነኛው
6
ነሐሴ 2012
ለግብይት ያገለገለ ኮሞዲቲ እንደነበር ድርሳናት ያስረዳሉ። ከዚህ ቀጥሎ ተወካይ ገንዘብ (representative money) የሚባለው ገንዘብ ተጀመረ። ወርቅና ብር ነጋዴዎች ለደንበኞቻቸው ደረሰኝ በመጻፍ፣ ያንን ደረሰኝ ደምበኞች በማምጣት በፈለጉት ሰዓት ወርቁንና ብሩን ማግኘት ቻሉ። ቀስ በቀስ ደረሰኙ በወርቁና በብሩ ቦታ ተተክቶ እንደ ሙሉ ገንዘብ መስራት ጀመረ። የወረቀት ገንዘብ ለመጀመሪያ ጊዜ ጥቅም ላይ የዋለው በሶንግ ስርወ-መንግስት (970 ዓ.ም. - 1276 ዓ.ም.) ዘመን በቻይና አገር ነበር፣ ብሮቹም ያወዚ ይባሉ ነበር፣አመጣጣቸውም ከላይ እንደተገለጸው የደረሰኝ ጽህፈትን ተከትሎ ነው። አውሮጳ ውስጥ የወረቀት ገንዘብ ለመጀመሪያ ጊዜ ጥቅም ላይ የዋለው በ1661፣ ስዊድን አገር ነበር። በዚህ ወቅት እያንዳንዱ ጥሬ የወረቀት ብር ወደ ተወሰነ የወርቅ ክብደት የሚቀየርበት ስሌት ነበረው ። በ1946 ዓ/ም የመጀመሪያው ክሬዲት ካርድ ለአለም ተዋወቀ።
ዲጅታል ገንዘብ ዲጂታል ገንዘብ ከአካላዊ ገንዘብ (physical currency) ማለትም ሳንቲም ፣ ወረቀት ገንዘብ ... በተቃራኒ ዲጂታል ላይ የተመሰረተ ነው ። ይህ የገንዘብ አይነት ከአካላዊ ገንዘቦች ጋር ተመሳሳይ ባህሪያትን ቢያሳይም ቅሉ ፈጣንና ቅጽበታዊ እንዲሁም ድንበር አልባ የሆኑ የገንዘብ ዝውውሮች መገለጫ ባህሪዎቹ ናቸው ። ምናባዊ ገንዘቦች (virtual currencies) እና ክሪፕቶከረንሲዎች የዲጂታል ገንዘብ አይነተኛ ምሳሌዎች ናቸው ። ልክ እንደ አካላዊ ገንዘቦች ሁሉ እነዚህም ገንዘቦች የተለያዩ ቁሳቁሶችን እና አገልግሎቶችን ሊገዙ ቢችሉም አንዳንድ ጊዜ ለተወሰነ ማህበረሰብ ለምሳሌ ለመስመር ላይ ጨዋታ (online game) ወይም ማህበራዊ አውታረ መረብ (social network) ላይ ብቻ የተገደቡ ሊሆኑ ይችላሉ ።
ዲጂታል ገንዘብ የገንዘብ አቅርቦቱን የሚቆጣጠር አንድ ማእከላዊ አካል ሲኖር የተማከለ ዲጂታል ገንዘብ ይባላል ። ዴቢት ካርዶች እና ክሬዲት ካርዶች የተማከለ ዲጂታል ገንዘብ ምሳሌዎች ናቸው ።በተቃራኒው የገንዘብ አቅርቦቱ ቁጥጥር እና መገኛ ከተለያዩ ምንጮች ከሆነ ደግሞ ያልተማከለ ዲጂታል ገንዘብ ይባላል ። ክሪፕቶከረንሲዎች ያልተማከሉ ዲጂታል ገንዘቦች ናቸው ፡፡ በቀጣዩ ዕትም በወርቅ እና መሰል ሸቀጦችም ሆነ በመንግስታት ስላልተደገፉት እና እውቅና ስላልተሰጣቸው በመንግስታዊ ተቋማት እና ማእከላዊ ባንኮች ስላልታወጁት እና ዋጋቸው በእነዚህ ተቋማት ስላልተበየነው እንዲሁም በማንም ቁጥጥር ስር ስላልሆኑት እና ባለቤት ስለሌላቸው ምን አለፋችሁ በጥቅሉ አዛዥ ናዛዥ ስለሌላቸው እና የዘመናችን ክስተት ስለሆኑት ክሪፕቶከረንሲ ስለሚባሉ ዲጅታል ገንዘብ አይነቶች እናወራለን። ቸር እንሰንብት። (ልዑልሠገድ ጥላሁን አ.ሳ.ቴ.ዩ 4ኛ ዓመት፣ ኮምፒዩተር ሳይንስ እና ምህንድስና ተማሪ )
Vol. 3
ዕድ
amPhi
3D PRINTING Yafet Girum
3D printing is a process of making three dimensional solid objects from a digital file. 3D printing is when 3D solid objects are made from a model on a computer. 3D printin is done by building up the object layer by layer and also called Additive Manufacturing because the object is created by laying down successive layers of material until the object is created. Each of these layers can be seen as a thinly sliced horizontal cross-section of the eventual object. 3D printing is the opposite of subtractive manufacturing which is cutting out / hollowing out a piece of metal or plastic with for instance a milling machine or a laser engraver. 3D printing enables you to produce complex shapes using less material than traditional manufacturing methods. Usually, 3D printers use plastic, because it is easier to use and cheaper. Some 3D printers can 3D print with other materials, like metals and ceramics.
I have a 3d printing on demand business where customers provide me with a 3D model or a sketch then I process the models and give the customers the actual printed object. If you want to learn more you can find my contact below. Currently I am working with the physicians and doctors at Millennium Hall Emergency Hospital. I design, 3d print and donate the parts they need for either the ventilators or to increase the protection and comfort of our front line defense against this merciless pandemic. Since I have the deep desire to play my part in the fight against Covid-19, I am donating the parts I print for free. I am also starting a makers group and a movement to help in organizing and donating parts called “Addis Fighting Covid”. If you are a maker or you know someone who is, especially interested in 3d printing or donating 3d printing filament, please feel free to contact me and let us discuss how we could use your help. Email: [email protected]
7
ነሐሴ 2012
Applications of 3D Printing 3D printing encompasses many forms of technologies and materials as 3D printing is being used in almost all industries you could think of. It’s important to see it as a cluster of diverse industries with a myriad of different applications. A few examples: easy quick fixes and replacement to almost any plastic part, lithophanes, clear aligners / braces in dentistry, eyewear, architectural scale models & maquettes prosthetics, movie props and figurines, design (lamps, furniture etc.), reconstructing fossils in paleontology, replicating ancient artifacts in archaeology, toys for children, wedding gifts (Yafet Girum, Adama science and Technology University Computer Science and Engineering Student)
Vol. 3
ፈታ ብዕር
amPhi
Jeequmsa /midhaan mana kessaa Ayantu shallama
Yeroo kanatti biyya keenya itoopiyaa kessatti gudeeddi durba umriin isaanii heerumaaf kan hin geenye maatiidhumaa abbakoo jeetu irra gara jabeenyaan midhaan haamaa ta’ee qaqqabaa jira. Karaa biraan immoo dubartooni keenya butama jirru. Caallisuun kenya obboleetti keenya midhaa jirra. Akka biyya kenya itoopiyaatti qofaa ji’a 2 kessatti dubartoonii umriin isaani heerumaaf hin qaqqabnee akkasumas daa’iiman 101 ta’aana akka gudeedaman ni beektu?waanti kun haama yoomitti callifama? Waantoota akkasii yommu ilaalu midhaan qaqqabu baay’eedha. Haa ta’uu malee midhaa / jeequmsa mana kessa jechun moggasuu dandenya .mee waa’ee midhaa /jeequms mana kessa haaman beekuu isiinif caqasa. Jeequmsa /midhaan mana kessaa ( Domestic Violence ) Jeequmsi/midhaan mana kessa kun Maddeen dhala nama irratti raawwatamu hedduu hamaadha. Jeequmsaa fi midhaa yommu jeenu karaa adda addaattin gargar baasuun ilaalu dandeenya. Jeequmsa kan jeenuun kun kan abbaan hin himanne kan namni namaa hin beekne waan ta’eef hedduu namni waan hin xiyyeeffanneef kan hubuu fi kan miidhuu dha.Miidhaan kan jeenuun kun immoo mana keessatti warruma namoota walitti dhufan gidduuttis ta’ee nama didaatiinis haala adda addaatiin kan qaqqabuudha. Miidhaan kun namoota warra jaalallee gidduu ykn karaa ( intimate partner violence) maatii gidduuttis ille kan uumamuu dha. Miidhaan mana keessaa kun heedduminaan dubartoota iratti haa baay’atu malee warra dhiiraa irrattis illee ni muudata.Akka biyya kenya itoophiyaatti dubartoota daa’iman midhaan itti qaqqabee irraa ansee daa’imman dhiraa 57 ta’aan umriin isaani 15 gadii ta’aan balaa kanaaf saaxilamanii jirru. Garuu yoo qo’annaan walitti qabame keessaa ilaalamu -Dubartiin harka 3 (sadi) keessaa harki tokko (1) miidhaan irra gaha, dhiirri harka 7 ( torba ) keessaa harki 1( tokko) miidhaan irra gaha jechuudha. Haa ta’u malee akka biyya Itiyoophiyaatti karaa hedduun baa’inni kan dubartiitu
8
ነሐሴ 2012
caala. Miidhamni illee qorannaa irra jiru miidhama Du’aa, Ajjeechaa ,Gudeeddii/ Butii ,Miidhaa barumsa argachuu dhabuu ,Miidha Ofitti amanamummaa dhabuu fi k k f, kan argarsiisan dubartii irratti jechuudha. Heddumminaan rakkowwan kanaaf sababa ta’aan Aadaa,Amantiin akkasumas hanqina walqixxummaa dhiiraa fi dubaraatiin fi kan kana fakkaataniin kan dhufaniidha. Miidhaanifi jeequmsi jaalalloo gidduutti ta’u akka saayinsiitti haala 2 ( lamaan) ta’a. Miidhaa Qaamaa fi jeequmsa Sammuuu/ Yaaduu.Miidhaa Qaamaa kan jennu miidhaan kan itti argamu qaamaan yommuu ta’uu dha. Midhaan qaamaa kun madaa ykn gooddanisaan qaama irratti argamu kan namni didaa wanta arguu dand’uudha. Miidhaan kunis kan qaqqabu haalota adda addaatiini, Rukuchaadhaan yommuu ibsinu haala badaa ta’een uleedhaanis ta’ee harkaan reebicha cimaa ta’e kan nama irra geessisuudha. Gudeeduu- Kana jechuun fedhii shamarree sanaa malee dirqiidhaan walquunnamtii saala irratti raawwachuu jechuu dha. Kunis Kan uumamuu danda’u haala lamaan ta’a. Haalli 1ffa haadha manaa fi abbaa manaa gidduutti kan uumamuu dha. Kunis fedhii abbaa manaa qofa yommuu ibsuu fi fedhii haadha manaa osoo hin gaafatin walquunnamtii saalaa uumamu dha.Haalli 2ffaa n ammo durba maatii ishee waliin jiraattu butuudhaan fedhii ishee malee gudeeduudha. Kunis baay’inaan dubartoota umuriin isaanii heerumaaf kan hin geenye irratti wanta baay’inaan gahuudha. jeequmsa sammuu irra qaqqabu yommuu jennu, jeequmsi dubara sana irratti argamu ifa bahee wanta argamu osoo hin ta’in ykn qaama irratti miidhaan sun wanta mul’achu hin dandeenyeedha. Akkasumas jeequmsi sammuu kun haala 3’n ibsuu ni dandeenya. Inii jalqabaa Namni kan arguu hin dandeenye mana keessatti kan ta’amuu fi haala ,Arrabsoo ,Haamilee gadi buusuu ,Balleessaawwan hunda dubartii sana irratti maxxansuudhaan karaa sammuun ishee akka dhiphatu kan ishee taasisuudha. Itti ansee immo jeequmsa sammun qabeenyaa ishee irratii qaqqabsiisu
ta’ee Dubartiin sun akka baatee hin hojjanne gochuu ,Qabeenya maatii keessa jiru ykn qabeenya haadha manaafi abba mana gidduu jiru akka Dubartiin sun seeraan akka itti hin fayyadamne gochuu, Qabeenya waliin horatan seeraan ala dhiirri akka itti fayyadamuu gochuudha. inni dhuuma immoo jeequmsa yaadaatti. jeequmsa yaaduu akka hin dandeenye kan godhuu dha. jeequmsi kunis dubartiin sun yaaduu hin dandeessu jechuun , Maatii keessaas ta’ee hadha manaaf abba mana gidduutti jireenya jiraatan irratti yaadni ishee kennitu akka fudhatama hin qabne gochuu,hawaasni jiru sababoota adda addaatiin akka dubartiin sun ofitti hin amanne kan godhaniidha. Haa ta’uu malee fedhii malee diirqiin walqunnamtii saalaa dubartii sana irratti raawwatu kun jeequmsa sammu ilee haala baddaa ta’een fiduu danda’a. Miidhan/jeequmsi kun sababni itti dhufan wantoota akka biyyaatti illee dubartoonni walqixummaa dhiira faana akka hin qabne haawaasnii jiru aadaa godhatee waan jiruufi dha. Dubartiin miidhaan fi jeequmsi akkasii kun itti qaqabaa jiru yoo jiraatan ykn karaa dubartoota kana gargaaruf gorsa adda addaa argachuf akkasumas waa’ee obboleettikootti sagaleen qaba yoo jeettan karaa (Ayantu shallama Barattuu geology science waggaa 3ffa ASTU)
Vol. 3
ፈታ ብዕር
amPhi
When they see us Kidist Abebe
One story: two different events, in two different worlds. America, Harlem, April 19, 1989 “Kevin right?... I saw you that night at the police station.” Raymond “Who are you?” asked Kevin. “Raymond” “I wandered who Raymond was” Youssef “That is when she got you?” Raymond asked Kevin Kevin exhales… “nah… man, um… I don’t know nothing about it. A cop… a cop hit me in the park.” “I saw that … with his helmet… I am Tron” … I am Cory, the 5th one. I am 16 while my friend Youssef and Raymond are 15 and Kevin and Antron are 14.we are convicted felons. We committed rape on a white woman. I went to the police station so Youssef won’t be alone. They said they needed him for some questioning. I went to the police station so my friend won’t be alone but I never came back out of it. Police station became my forced confession of raping a white woman, and then a convicted felon who went to adult prison at the age of 16.
Ethiopia, 2020 A new virus assaulted the world. The first covid-19 case found in Ethiopia was on February 11th. After a month schools were closed, people started working from home, social distancing happened. Something else also happened, rape.
This is how a grown woman feels when a man assaults her. Now imagine a little girl watching her dad with love in her eyes when he puts her to bed and then imagine her confusion when the fly of his pants are getting unzipped… I will say no more. For these of you who can imagine the pain of this little girl or any other woman who is being insulted. Assaulted, raped and lets not forget the boys who are raped, while in our country this wouldn’t be possible few decades ago. Let your voices be heard. Let’s be the change we say we need. Let’s see what they say when they see us. Let’s see the answer to the change of our voice. Thank you.
WHEN THEY SEE US
9
ነሐሴ 2012
More than 100 kids were raped in those 3 months only in Addis Ababa, the capital city of Ethiopia. The numbers are not known on the regional states of the country. Some of those girls were raped by their fathers. Boys being raped, another disturbing tale. A tale that shouldn’t have happened in this God worshipping country. I will let you readers compare the discrimination of these two countries. While in America 14 years olds are being imprisoned for life with the crime of rape because of the color of their skin, in Ethiopia, kids are being raped by strangers and some their fathers and still, no law is working on bringing justice to those fallen angels. “I feel dirty when a man assaults me on my way to work. No shower or soap can wash away how his eyes lingered on my body…”
(Kidist Abebe, Adama Science and Technology University, Architecture student)
Vol. 3
ፈታ ብዕር
amPhi
Hiriyaa
Daraara katamaa
Harka fuudhe kabajamtoota hordoftootaa fi jaalattoota barruulee Amfi! Hiriyyummaan seenaa wagga heedduu qaba. Yeroo bara durii kaasee ilmi namaa nama akka ofiitti amanu, icciitii waliin qoodu, waliin jiraachuuf kayyeffatu, kana qofa osoo hin taane lubbuu isaaf kennu barbaaduun waan baramedha. Warri keenyi bara durii jiraatan, hiriyyummaan hangam jabaaataa akka ta’e waan hubataniif, yeroo waa’ee hiriyyummaa mammaakan akkas jedhu, “hiriyaa kee naaf himi eenyummaa keen sitti hima”. Maarree hiriyyummaan yeroo bara durii jalqabe kun jabaatee, hiikaan hiriyyummaaf kennamu irra caalaatti bareedee itti fufeera. Haata’u malee, hiriyyummaa yommuu jennu hundumtuu gaarii ta’a jechuu miti. Akka yaada kootti osoo hiriyyuummaa gosoota sadiitti qoodnee, hiikaa isaa qofa osoo hin taane, kaayyoo, yeroo fi xumura isaa hubachuuf nu gargaara jedheen amana. Kanaaf, hiriyyummaan:- hirriyyummaa gaarii, hirriyyummaa badaa fi hiriyyummaa gosa lamaan armaan olii jalatti hin ramadamne ta’uu danda’a. akkas jechuuf ija akkan jabaadhu kan na taasise yommuu lafa kanarra jiraannu anis ta’e isin, waa’ee hiriyyummaa waa heedduu hubattanii ilaaluu dandeessaniittu jedhee waanan yaaduufi. hiriyyoonni tokko hiriyyummaa yeroo jalqaban baay’ee walitti waan siqaniif namoonni naannoo isaanii jiraatan eessa ga’uu jedhanii osoo eeganii, hiriyyumaan isaanii yeroo xiqqootti bakka yaaadame osoo hin ga’iin kichuutti murama, kanaafi
10 ነሐሴ 2012
oromoon yeroo mammaaku “jaalalli wajagsaan jibba madaqsaa fida” kan jedhu. yeroo tokko tokko, namni hiriyaa nu godhatu kaayyoo ofii isaa barbaaduuf qofaaf nutti siquu danda’a, jechuun hiriyyuummaa qama isa tokkoof qofa faayidaa argamsiisu, kaayyoon qaama tokkoo osoo hin baramiin dura hiriyyummaan isaanii hiriyyuummaa gaarii fakkaata hanga qaamni kaayyoo qabaate sun kaayyoo itti isatti siqeef galmaan ga’atutti. Rakkoon isaa gaafa kayyoon nama kanaa qaama isa biroon beekamedha. Hiriyyummaan isaanii kan dhugaa waan itti fakkaachaa tureef, akkamitti anaan kaayyoo mataakeef meeshaa na godhatta, akkamitti anaan na mooqsita/ gowwoomsita jedhee ofitti aruu jalqaba. yeroo kana akkuma amala nama fi kaayyoo hiriyaa irraatti hundaa’ee tokko tokko, hiriyyaa isaa isa booda arguu hin barbaadu, kaan immoo dhiifama godhee hiriyyummaa isaanii itti fufuuf carraaqqii godha, kan biroo immoo, waa’ee nama kanaa namoota birootti lallabuun akka hiriyyaa biraa hin arganne godhuu kan barbaadan jiru, gama biraan immoo, hiriyyaa isaanii yookiin of ajjeesuuf kan yaadanis hin dhabamani. Namoonni waan akkasii irra ga’e waa’ee hiriyyummaa waan gaarii yaadu hin barbaadan. Kanaaf hiriyyummaan namaa hin barbaachisu jedhu. Irra darbanii mammaaksaan akkas jechuun dubbatu “nama amanuun awwaalaniiti” jette jeedalli. Hiriyyaan hundi garuu harka isa nyaachise hin nyaatu. Hiriyyummaan dhugumaan hundeeffame baroota heedduuf jiraata, yeroo rakkoo
waliin rakkatanii, yeroo gammachuu waliin gammadanii, waan yaada itti ta’e waliif qoodanii waliin jiraatu. Anis carraa kana argadhee kunoo hiriyyoota koo lamaan waliin yeroo barnoota jalqabnee kasee hanga ammaatti kan waliin ta’uu dandeenye, hiriyyummaan keenya ammas akka itti fufu abdii guddaan qaba. Barreefama kanas akkan barreessu kan na kakaase isuma kanadha. Haa ta’u malee, Hiriyyummaan gaarummaa yookaan yarummaan isaanii hin beekamnes hin dhabamu, hiriyyummaan kaayyoo hin qabne isa kanadha! Nuti hiriyyoota jedhanii osoo yaadanii gadhummaa walii nama biraatti haasa’uu, hiriyyoota jedhanii osoo yaadanii waan hiriyyaa isaanii miidhu raawwatu, waan kana hunda osoo beekani immoo hiriyyummaa isaanii itti fufu. Hiriyyummaan keessan hiriyyummaa gaarii akka ta’u isiniif hawwa! Rabbi hiriyyummaa gadhee fi kaayyoo hin qabnerraa isin haa baraaru! Isinhoo waa’ee hiriyyummaa yaada qabduu? Yaada keessan nuuf qoodaa. @amfi Horaa bulaa! (Daraara Katamaa, barataa Computer Science and Engineering YSTA)
Vol. 3
ፈታ ብዕር
amPhi
Insecurity
Edelawite Tsegu
Is something we all suffer from ... We all hate something about us....? Some of us hate our looks, some of us hate our body and some of us even hate our personality ... We try to hide them our body with close, our face with makeup ... some even go to the length of getting them surgically replaced ... It’s not that am against wearing a good close or makeup, it just shouldn’t be used to hide who we are physically but to make us look better ... I believe the concept of beauty is what leads us to it.... As long as there is beautiful there is ugly... When there could have been all sorts of beautiful ... Plus size beautiful, skinny beautiful, long beautiful, short beautiful... but the world have a standard of what a person should be and shouldn’t be and we’re all expected to live up to it ... I asked few people what they hate about themselves Some of them don’t want to talk about it and others are ashamed of it... I myself have some things I hate about myself which is hard to revile ...
11 ነሐሴ 2012
This is how bad the world is screwed up ...we act like beauty could change the world “the nose of Cleopatra if it had been short the face of world would have been changed” is what they say, like her beauty is the only thing that matters ... We are the once causing it ignoring each other like what we have don’t matter. Everyone of us have something good in us, something that’s worth so much, something that can change the world... So focusing on what we don’t have is wasting a great resource which is us. Someone once said “ sometimes our thoughts are blocked by so much insecurities they create lies we believe.”
... and I say insecurities are lies, and our beauty is the truth ... you may not be cute, you may not be sexy, you may not be stylish but everything you are in everything you can be all there is within you that’s your beauty.... The world always has something to say skinny - anorexic, tick - fat.... So stop trying to change it just love it in live it.... I believe getting too much attention can make you insecure too. Like affirmative action which makes you feel like a guest in your own world. It sends a message saying “you can’t do this alone so I’m going help you”.... I’m not saying helping people in need is wrong but let’s stop treating them like they are broken like they can’t stand by themselves.... Because they can we all could as long as we believe we can.... (Edelawite Tsegu , Material Science and Engineering Student, ASTU)
Vol. 3
የኔታ
amPhi
ወጣትነት እና ቁጠባ ቤተልሔም እርዳቸው ልብ በአርባ ዓመት ብር በሃያ ዓመት ይላሉ የሀገራችን ሰዋች ሲተርቱ።ይህ በየትኛውም የህብረተሰብ ክፍል የሚሠራ አባባል ነው ቢባል አያጣላም።ምክንያቱም በወጣትነት ጉልበቱ እያለ ተሯሩጦ ሠርቶ ጥሪት መቋጠር የተሳካለት ራሱን ለመቻል ሲሯሯጥ በዚሁ እድሜ እንዲሁ ያገኝውን ከእጅ ወደ አፍ አይነት እያባከነ ዓላማውን ለማሳካት የሚሳነው ቁጥሩ ቀላል አይደለም በእርግጥ ትንሽ የማይባሉ ቤተሰቦች ልጆቻቸውን ገና ከለጋ እድሜያቸው አንስተው የገንዘብ አያያዝንና አወጣጡን ለማለማመድ ይጥራሉ። ለመሆኑ ወጣቱን ቁጠባ ባሕሉ እንዳያደርግ ያደረገው ነገር ምንድን ነው ? ምን ያህልስ ይቆጥብ የሚለውን ጥያቄ ለመመለስ ያክል በመጀመርያ ቁጠባ ምንድን ነው የሚለውን ሀሳብ ብናነሳ ጥሩ ነው። ቁጠባ ዛሬ ላይ ሆነን ነገን በማሰብ ከምናገኝው ገቢ በተወሰነ መጠን ወይም ቀንሰን የምናስቀምጠውና ለፍጆታ የማናውለው ገንዘብ ነው ።ቁጠባ ለነገ የተሻለ ህይወት፣ ለእርጅና ዘመን ፣ ወደ ፊት ለሚያጋጥመን የገንዘብ እጥረት ፣ ሊያጋጥሙን ለሚችሉ አደጋዎች መቋቋምያ ...ወዘተ ፍላጎቶቻችን ሁሉ ለመጠቀም እንድንችል ዛሬ የምናስቀምጠው ገንዘብ ነው።ቁጠባ ለኢንስትመንት ብቻ ሳይሆን ከላይ የገለጽናቸውን የወደፊት እቅዶቻችን ለማሳካት ሆነ ለሚያጋጥሙን ችግሮች መውጫነት ሊያገለግለን ይችላል። የምንቆጥበውን ገንዘብ በባንክ ብናስቀምጥ የተሻለ ነው።ብዙ ጊዜ ወጣቱ ወይም በሀገራችን በተለይም በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ሰዎች ስለ ቁጠባ ጠቀሜታ ቢረዱም የምናገኝው ገቢ አነስተኛ ስለሆነ ከዚህች ላይ እንዴት መቆጠብ እንችላለን ይላሉ ።እውነታው ግን መቆጠብ ያለብን ከዚህችው አነስተኛ ከሆነችዋ ገቢያችን ላይ መሆኑ ነው።ቁጠባ የህይወታችን አንዱ አካል አድርገን ማየት ካልቻልን የወደፊቱ ጊዜ የእኛ እንዳይሆን ካሆኑ እየወሰንን ነው።ገንዘብ ስናገኝም ፍላጎታችን በዚያው ልክ እያደገ ስለሚሄድ ቁጠባን መጀመርያውኑ ባህልአችን አድርገን መሄድ ካልቻልን የፈለገውን ያህል ገቢያችን እያደገ ቢሄድ ልንቆጥብ አንችልም።ስለዚህ ካለችን
12 ነሐሴ 2012
አነስተኛ ገንዘብም ቢሆን መቆጠብ አስፈላጊ እንደሆነ ሁሉም ወጣት ግንዛቤ ሊወስድ ይገባል። ምን ያህል ይቆጠብ? ይህን ጥያቄ ብዙዎች የሚጠይቁት ሲሆን ስለቁጠባ መጠን ይሄንን ያህል ወይም በዚህ መጠን ይሁን የሚባል ፎርሙላ ባይኖረውም ብዙ የኢኮኖሚ ( የምጣኔ ሀብት ) ባለሙያዋች ከገቢያችን ከ10%እስከ 20% የሚሆነው መቆጠብ አለበት ይላሉ።ይህ እንግዲህ ትንሽ ከሚያገኝውም ብዙ ከሚያገኝውም ነው።እና ወጣቶች የቁጠባን አስፈላጊነት ተረድተው ቁጠባን አቅማቸው በፈቀደላቸው መጠን ባህልአቸው ማረግ አለባቸው።ቁጠባ የምንቆጥበው መጠን ላይ ሳይሆን ቁጠባ ላይ ያለንን አመለካከት መቀየር መቻላችን ላይ ነው። አስተሳሰባችን ከተቀየረ ትንሽም ቢሆን የምንቆጥበው ነገር ዋጋ አለው ።ትንሽ መቆጠብ ስንችል ደግሞ ብዙ መቆጠብን እንማራለን ። ምክንያቱም ቁጠባ አንዴ ከጀመርን ከምናገኝው ጥቅም እየተበረታተን ልንሄድ ስለምንችል ነው መቆጠብ ካልጀመርን ግን መቼም መቆጠብ አንችልም ።አንዳንድ ወጣቶች ቁጠባ መቆጠብ ያለበት አነስተኛ ገቢ ያለው ነው የተሻለ ገቢ ያላቸው ሰዋችማ የተሻለ ሀብት አላቸው ይላሉ ።በእርግጥ አነስተኛ ገቢ ያላቸው ሰዎች መቆጠብ ካልቻሉ ነገንም እንዲሁ ይቀጥላል።ነገን የተሻለ ለማድረግ የግድ መቆጠብ እንዳለባቸው እንረዳለን።ሆኖም ግን የተሻለ ገቢ ያላቸው ሰዎች አይቆጥቡ ማለት አይደለም ።ምክንያቱም ነገን ማወቅ ስለማይቻል ነው።ዛሬ ያለን ገንዘብ በተለያየ ምክንያት ነገ ልናጣው እንችላለን ።ከዚህ አይነት አጋጣሚ ለመውጣት ቁጠባ አስፈላጊ ነው።ስለዚህ ማንም ወጣት መቆጠብ እንዳለበት ግንዛቤ ሊኖረው ይገባል። ቁጠባን ባህላችን እናድርግ። (ቤተልሔም እርዳቸው የሐራምቤ ዩኒቨርሲቲ የንግድ አስተዳደር የደህረ-ምረቃ ተማሪ)
Vol. 3
የኔታ
amPhi
ህልም ተስፋ ብዙወርቅ
አሻም እንደምን አላችሁ በዚህች በራሴ ግጥም ጉዟችንን ሀ እንበል
ህልም የተቀን ተቀን መሻት በዕዝነ ልቦና የስሜት ማሰሮ የመሻት ጠብታን አቁሮ አሳድሮ ከማሰሮው ሞልቶ አልፎ ሲኩረፈረፍ ህልም ማለት ፍቺው በሌት እንቅልፍ መሃል የቀን ሻትን ማረፍ ጥላ ሆኖ ከርሞ ልብን የሸፈነ ጥቀር ቅርፊት መቅፈፍ ህልም ማለት ፍቺው በሰመመን መሃል ሲደግሙት ማደር ነው የቀንን ተጋድሎ በሃሳብ መድግም ነው ጭንቁን የቀን ውሎ ብቻ ብሎ ማመን ብቻ አድርጎ ማመን በዚህ ስልጡን ዘመን ልክ ይሆናል መሰል ስልጣኔ የደረጀ እና ስርዓታዊ እውቀት ማሳያ ነው። ዘመነኛው ስልጣኔ በምድረ-አውሮጳ ሲነሳ የህዳሴው ጠንሳሾች ወደ ጥንት ግሪክ እና ሮማዊያን ተመልሰው ነው እርሾ ያገኙት። እኛስ ካለንበት አዘቅት ለመውጣት እርሾ የት እየፈለግን ነው? ወይስ ያለእርሾ ‘ማቡካት’ ጀመርን? ነባሩ እውቀታችን መጠየቅና መመራመርን ከብዙሃኑ ፊት አርቆ ማመን እና መቀበልን ብቻ ፈቅዷል። ዘመናዊው እውቀት ደግሞ ምክንያት እና ውጤትን ምሰሶው አድርጎ የቆመ ነው። ይህ ዘመናዊ ትምህርት በሀገራችን ሲተገበር በአዋጅ መልክ ከመንግስት ወደ ህዝብ የተጣለ እንጂ እንደባህል በሒደት ከህዝብ ወደ መንግስት የወጣ አይደለም። ይህም ውሎ አድሮ በነባሩ እውቀት እና በአዲሱ መሃከል ግጭት ፈጥሯል።
13 ነሐሴ 2012
በዘመናዊ ትምህርት ውስጥ ያለፉ ሰዎች በጊዜ ሒደት ራሳቸውን ከወጡበት የባህል፣ እምነት እንዲሁም እውቀት ጋር ለማስተያየት ፍቃደኛ ሳይሆኑ ቀሩ። ነባሩ እውቀት እና ዘይቤ ሁሉ ኋላቀር እና ከዘመን ጋር ማይራመድ ተደርጎ ተፈረጀ። በዚህም ሁለት የእውቀት አካሄድ በጉልህ ተፈጠረ። ነባሩ እውቀት እና ዘመናዊው ትምህርት ከባድ ጉዳዮችን በጋራ መፍታት ቀርቶ አንዱ ለአንዱ ያለዋጋ እንኳን የሚሰጡትን በረከት ሳይሰጣጡ ሳለአይሰጥ ሆነው ዘለቁ። ይህ ኩርፊያም ዘልቆ ዛሬ ደረሰ። አንዱ ሌላኛውን እያጣጣለ እና እያናናቀ። * * *
እንዲህ ወዲህ ደግሞ አፈር፣ ውሃ እና አየር የቆሙት ስጋ ሆነውለት ማገር ለብሶ ሚዞር መንፈስ ነብስን ተመስሎ የጎደለ ግብሩን በስጋ ታጅሎ፣ መገኘት ቢያቅተው ከለስላሳው ስጋ ለስላሳ ተፈጥሮ፣ በትይዩ ካለው እሳታዊ ህይወት እሳታዊ ኑሮ፣ ህልም ማለት ፍቺው የሚያገናኝ ድልድይ በአብርኾት አሻግሮ። እኔ ብዬ አምናለው ልክ እንደፊቶቹ እናዳበው እናደመው እኔ ቅጠል እንጂ ቅርንጫፍ አይደለው የትልቁ አድባር ፣የትልቁ ዋርካ፣ ተራ ዘለላ ነኝ ተቀንጥሼ ምወድቅ በንፋስ ስነካደ እና ታዲያ እኔ ማነኝና ከስሪ ኑባሬ፣ ከግንዱ ዘልማድ፣ ከቅርጫፍ ፉካ፣ መንገዴን አርቄ ህይወቴን ለውጬ ሃሳቤን ምላካ። *
*
*
ምንም ነገር ከምንም ነገር ነጻ አይደለም። ሁሉም የተያያዘ ነው። የቱንም ያክል በዘመናዊው እውቀት ብንልቅ የአባቶቻችን ፣ የእናቶቻችን ልጆች ነን። እዚህ ያደረሰንን መንገድ ልናከብረው ይገባል። በ’በአዕምሯችን ስርቻ’ የጣልነውን ነባር እውቀት አውጥተን ተገቢውን ክብር እንስጠው። ሀገር በቀሉ እውቀት መቼም ተዋርዶ እና በልዞ አያውቅም። እኛ በተውነው መጠን ተዋርደን ለማንነት ቀውስ ተጋለጥን እንጂ። ከአስመሳይነት እና ጥቅመኝነት ተላቀን እንመርምረው። በአከበርን ቁጥር ክብር መልሳችን እንደሆነ መጠርጠሩስ። በዘመን ቅብብሎሽ እዚህ የደረሰው የአስተሳሰቦች ግጭት እዚህ ጋር ከመሰረቱ ሊፈታ ይገባል። የሎሬት ጸጋዬ ገ/መድሕን በተለይም በገጣሚነት ያሳዩን ከፍታ የመጡበትን መንገድ በእውነት ማክበራቸው መሆኑን የተረዳነው አይመስለኝም። ወደ ርዕሴ እና ግጥሜ ስመለስ ህልም ፈቺ አያት ያለው ልጅ የህልምን ዋጋ ሳያውቅ ሲቀር ያሳዝናል። ህልም ከቅዠት እና ከቀን ትውስታ በዘለለ በገሀዱ እና በረቂቁ ዓለም መሃል ያለ የአብርኾት ድልድይ ነው። የሚፈታ ህልም ይታያችሁ። አይቀጥልም
Vol. 3
የኔታ
Sa’a Ibidda dhalte
Dajanee Gaaddisaa
Karaa itttiin hubannuu fi hiiknu gargar ta’uus hadhaa fi mi’aa Addunyaa namni hin dhandhamne waan jiru natti hin fakkatu. Gama tokkoon namumatu madda rakkooti, gama kaanin immoo fala. Isa tokko balleesse kan biraatu tolcha. Isa kan biraa dabse kan hafetu sirreessa. Kun amaluma jiruuf jireenya Addunyaa kanaati. Haaluma qabatamaa biyya kanaatin yoo ilaalle wantoonni guyyaa guyyaan argaa ollu, “biiftuun abbuma ilaalef sirriidha” ejjennoo jedhuun nu gaha. Akkuma beekkamu biyya kana keessa Mootummaa lamaafi Sanaa oltu jira, keessa beekumsaan jechuu kooti. Inni kaan hojii eebbifamaadha, uummata biyya kootiif gammachuu uuma jedhee dalagu, isa kaanif gantummaadha. Biyya gurguruudha. Aantummaa uummataa dhabuudha. Yakka guddaadha. Faallaa isaatin Mootummaa isa lammaaffaa biratti yaadni fi gochi eebbifamaa jedhamee yaadamu isa duraa birattti faallaa isa duraati.
14 ነሐሴ 2012
Amma rakkoo kan ta’e Kuta hawasaa (namoota) jidduu kana lamaan jiraniidha. Kannee mootummaa hundaa Mootummaa isaanii godhanii fudhachuufis dhiisuufis mirga hin qabne. Warraa jiruuf jireenya isaanii waliin naanna’aa oolan. Warra rakkoo uumuuf fedhiin hin qabnee fi isa uumameefis qaama furmaataa ta’uuf human hin qabne,…. Jiraachuuf jecha yoo yaada mootummaa isa tokkoo deeggaranii fudhatan mootummaa isa biro biratti diina ta’uuf deemu ….. Dubbiin dubbii “sa’a Ibidda dhaltee” taate, akka ‘in dhiifnef ilmoodha, akka ‘in arraabneef ibidda. (Dajanee Gaaddisaa, Dafqaan Bulaa)
amPhi
Vol. 3
ኪን
amPhi
የማትረባ ፍየል ዘጠኝ ትወልዳለች እነሱም ያልቃሉ እሷም ትሞታለች እዮብ ዘ ሐ
ድሮ ነው አሉ መቼም ‘ድሮ’ መስፈሪያ የለውም ያው ‘ድሮ’ ነው ጥጉ። ታዲያ በዚህ ድሮ ብዙ ፍየሎችና በጎች አንድ ላይ ታጉረው በሚኖሩበት ጉረኖ ውስጥ አንዲት ኮረዳ ‘ልታይ ልታይ አበዛች’ አሉ አሮጊት በጎችና ፍየሎች። መስክ ወርደው ሳሩንም ቅጠሉንም ሲቃርሙ እየጠፋች መሄድ አበዛች...ፀጉሯን ወደጎን ማበጠር ጀመረች...አንገቷ ላይም ዶቃ አሰረች...ይሄ ድርጊቷ የጉረኖ ፍየሎች እና በጎች የሳር ቅጠል ማባያ ሆነ... ‘ይሄ እዩኝ እዩኝ ደብቁኝ ደብቁኝ ያመጣል’ ተባለ ‘ ይሉሽን በሰማሽ ከጉረኖ ባልወጣሽ ‘ ተተረተ... ይቺ ምስኪን ፍየል ጉርምስናና ፍቅር አውሯት የሚታያትና የሚሰማት ከወዲያ ማዶ ጉረኖ ያለው የከንፈር ወዳጇ ድምፅ ብቻ ነበር። ምፅ!! ‘ምነው መክራችሁ አንድ ብትሏት’ ያለ አልነበረም እንደውም ‘ጆሮ ለባለቤቱ ባዳ ነው’ እያሉ ባዳ አደረጓት። የጉረኖው ጎረምሳዎች ነደዱ ‘ እኛ ለእሷ አንሰን ነው ወይ ‘ ቁጭት አንገበገባቸው። የጉረኖ ሴቶች ቅናት አጨሳቸው... በነገሩ ምንም ያልመሰላቸው ሽማግሌ ፍየሎችና በጎች ብቻ ነበሩ ‘እኔ ምሞት ዛሬ ማታ ቅጠል ሚደርስ ለፍስለታ’ን ተረተው ወደአረጀ ወጋቸው ተመለሱ።
15 ነሐሴ 2012
ወሬው ግን የፍየሏ እናት ጋ ደርሷል ግልምጫ አብዝታለች..አባት ፍየል አውቋል ቁጣ ቁጣ ብሏል ይብሱኑ ሰኔና ሰኞዋ ገጥሞ አርግዛ ቁጭ አለች። ለጥቂት ጊዜያት ልትደብቀው ብትጥርም ከቀናት ጋር አብሮ ሆዷ እየገፋ አልሆን አለ። አፍቃሪ ባሏም ከመስኩ ብቅ ካለ ሰነባበተ እንደውም ከማዶ ካለው ጉረኖ ተኩላ ገብቶ ጨረሳቸውም ሲባል ነበር። ጉረኖ ውስጥ ሹክሹክታና ፍርሀት ነግሷል ሆዳ መደበቅ ማይቻልበት ደረጃ ደርሷል። ከዚህ በፊት ሲጠይቋት ብዙ ቅጠል በልቼ እያለች ስታሳብብ እነሱም ‘ድንቄም’ እያሉ አሽሟጠዋል። አሁን ግን አልሆነም ስለዚህ በአንድ ጠዋት ጨርቄን ቅጠሌን ሳትል ሀገር ቀዬውን ጥላ፤ ጉረኖ አለሟን ሁሉን ትታ ወደ ሩቅ ተሰደደች ። ወደ ሩቅ ማንም ፍየል ወደማይደርስበት ማንም በግ ዝር ወደ ማይልበት ሩቅ ... ተጉዛ ተጉዛ የመውለጃ ጊዜዋ ሲደርስ ምጥ ሲጀማምራት ሊነጋጋ ሲል በቅርብ ወዳገኘችው ዋሻ ጠጋ አለች አጬልቃ ስታይ ባዶ ነው ወደ ውስጥ ዘልቃ ጎኗን አሳረፈች። ምጧም እየጨመረ አዋላጅ እና ደጋፊ በሌሉበት መውለድ የግድ ሆነ ሊነጋ አካባቢ ወልዳ ጎኗ አረፍ ከማለቱ የዋሻውን በር ጥላ ሸፈነው ድምፅም በቅርብ ርቀት ተሰማ። በለሊት አደን በለስ ያልቀናቸው ተኩላዎች ወደዋሻቸው እየተመለሱ ነበር...
ይህንን አሳዛኝ አጨራረስ በወሬ በወሬ የሰሙ የጉረኖ ኗሪዎች ይህን ተረት ከትውልድ ወደ ትውልድ አስተላለፉ ይባላል “የማትረባ ፍየል ዘጠኝ ትወልዳለች እነሱም ያልቃሉ እሷም ትሞታሉች”
Vol. 3
ኪን
amPhi
Room 203
Amanda Tirhas
“It was the first day of school and i was waiting for my father to take me to the bus and then i saw the war for the first time...” eva Woodrow Wilson high school was a school with high grade students, noble school. But then the volunteers integration was suggested and the school started accepting students from court’s order, students on probation, students who are trouble as the school stuff call them. Little did they know that the school ground would only be prison to the students and couldn’t protect them from the war on the streets. He lives in a box. Her mom died in a domestic violence. He deal drugs to support his mom because his dad is dead and his one and only brother is in jail for something he didn’t do. She have to lie to protect her kind because the only thing her dad thought her before he was dragged to prison was that she can’t go against her people and telling the truth would mean betrayal. He lived on the street for a year since he was evicted.
THOSE ARE TEENAGERS For those kids everyday is graduation since they live everyday as their last. So they live it protecting their own people, at least then it means they died with respect, they died warriors. It means they would be given the respect they know they will never get while they are alive. Little do they know after they are dead they will just rot on the ground and nobody won’t even know they were here let alone think of them as the warriors, little did they know this was not how respect was earned. Nobody cares about those lost souls. Even the school stuff think that trying to teach them is a waste in every possible way, they will just disappear one way or another.
They live a story worth telling, story written in a lot of books. But they don’t even know that someone before them have lived this life that is consuming them. No one cares enough to tell them that they can win this war that they can survive it. The stuff is more worried about a book being damaged than giving those wandering hearts a story of their own, book is better than their peace of mind. Room 203 was the prison they were cramped in. Their teacher had the belief that the real fighting should happen in a classroom so she fought them and then it became their heaven, a home they want to stay in forever, their sanctuary. It is amazing how much a little love can do. But for those of you who watched them being drawn into the dark and did nothing, for those of you who complained while they are the ones who have been caring the world’s burden on their shoulders, for those of you who made fun of their demons, for those of you who thought they were a misfortune to this world, who are you to insult, complain about those teenagers when you have done nothing to see them through it all??? Freedom writters review
16 ነሐሴ 2012
Vol. 3
ኪን
amPhi
Bad Old Days
Iman Mohammed
“But it’s not fair Mom, we’re just kids life shouldn’t be this hard but now, now it feels like the whole world gathers for destructing me.” Sofia started speaking. “Wait what? The whole world? For destructing you? Haha the world don’t even know you exist. You’re just one little girl nothing else. Sofi, you’re just 18 why are you so pessimist? “ “Naah this has nothing to do with being pessimist. Look at everything. Literally everything! Where ever you go you find nothing but sadness.” “That’s what life is dear. Why are you expecting for things to happen? Don’t. You’re just hurting yourself more. Now please stop this nonsense and eat your dinner.” That was my bigger bro speaking. I was 12 and I had no idea what they were talking about. The only thing I remember was that my siblings always argued while my mom had sat there and smile whenever one finished speaking. She’d never said a word. But her smile could tell that she had lived, that she had the answer for every issue they were arguing on. Now, after all those years I understand why Sofi and Musab never agreed & why my mom never spoke. Fool of me to think my mom had the answer to those questions. It took me years to understand that it was a smile of pain. A smile that says “yeah this is reality and Sofia my girl,
17 ነሐሴ 2012
welcome to the club.” Months passed since Sofi joined campus. One Sunday evening someone called me; “Hello Iman?” “Hello, who’s speaking?” “It’s Redi Sofi’s Dorm mate....She was fine the whole day she asked me if I could buy her dinner and when I come back...she’s gone “ I could hear her crying through the phone. “What does it mean that she’s gone? What’s wrong Redi tell me?” “ I don’t know I’m, She left a note she said...” ... 4 Years passed. We’ve never heard of her. “Do you think she’s still alive?” “Of course not but she was a happy girl. Her smile her jokes why would she do that to herself.” I heard my neighbors murmuring as I was passing by. Perhaps, in some way she was right when she said that the world gathered to destruct her. “If only you knew who she really was. If only you have been through the mighty storm with her” I said. I went back to my room and started reading her old journals. ~
[Why am I never able to smile like the rest? Why did he made me this way? Why do I feel like I never belong to this world? What is it that I’m missing? The burden I’m carrying right now.....] blah blah the sad notes never ended. I went to the last page to see if there’s something different. [Forgive me Sofia for I’ve killed you alive. But I promise I’ll make you proud soon. Very soon... Yours Truly: Sofia] ~ I smiled because I knew that wherever it might be Sofi has started living and that’s all I asked for. (Iman Mohammed, Medicine student at Jimma University)
Vol. 3
ኪን
amPhi
QUESTIONS
Kumneger Mesfine
Perché? Che cosa? Come?
Kumneger Mesfine (Urban planning at ASTU)
18 ነሐሴ 2012
Vol. 3
ፍልስምና
amPhi
ከበሩ በስቲያ በቃሉ ዋቺሶ
***
ክፍል አንድ***
እንደሚታወቀው፣ በአንድ ሃገር ሊኖር ለሚገባው ሁለንተናዊ እድገትና ልማት ዩኒቨርሲቲዎች የሚኖራቸው ድርሻ ከማናቸውም ተቋማት የተለየና የገዘፈ እንዲሁም ላቅ ያለ ነው፡ ፡ በዚህ ረገድ፣ ዩኒቨርሲቲዎች በየዕውቀት ረድፋቸው የሰውን ልጅ ኑሮ ለማሻሻልና እውቀትን ለማስፋፋት የሚጥሩ ሰዎች መገኛ በመሆናቸው፣ የየትኛውም አገርና መንግሥት ምሰሶዎች ናቸው ማለት ይቻላል፡፡ እንደዚህ ዓይነት ሰዎች ከሌሉት አንድ ኀብረተ-ሰብ የሚያስፈልገውን ንቅናቄ ሊያደርግና ሊሻሻል አይችልምና ነው፡፡ ከአርዕስቱ መገመት እንደሚቻለው፣ በዚህ በአራት ተከታታይ ክፍሎች ላቀርበው ባሰብኩት ጽሑፍ፣ የዚህ የክፍል ሁለት [ክፍል አንድ፣ በአምፊ ቁጥር 2 «የበሩ ገጨኝ ዘይቤ» በሚል ርዕስ መቀረቡን ልብ ይሏል።] ዓላማ ዩኒቨርሲቲ የሚለው ቃል ያለው ትርጉምና ያዘለው መንፈስ እንዲሁም የትምህርት መስፋፋትን ጥቅም ለማውሳት ሳይሆን፣ ስለ ዩኒቨርሲቲዎቻችን የውጪና የውስጥ ገጽታና ይዘት ጥምረት በተመለከተ አጭር ትዝብትና አስተያየቴን ለእናንተ ውድ የአምፊ ቤተሰቦች ለማካፈል ነው። የጀመርኩት በበር ነውና … እነሆ ስለሌላኛው ‹‹በር›› አወጋችሁ ዘንድ ይህ ሆኗል … እኔ የምለው፣ አንድ ከውጭ ሆኖ የሚያይ ሰው የዩኒቨርስቲዎቻችን [የመንግስት የሆኑት ላይ ብቻ ብናተኩር] መንፈስ እንደ መግቢያ በራቸው የኔ በሚሉት ኪነ ህንፃ እና ትምህርት ስርአት የተዋቀረ [በተለይም ከትምህርት ነጻነት አኳያ] ቢመስለው … የጠበቀውን ያገኝ ይሆን›***
19 ነሐሴ 2012
በአንድ ኪነህንፃ ምለው የተገዘቱ ይህ ኩነት በተለይ እንደ አ.ኢት.አ በ2ሺዎቹ የተከፈቱት ዩኒቨርሲቲዎቻችን በኪነህንፃቸውም ጭምር እንደ መንታ ተመሳስለው የመታየታቸው ሚስጢር ነው። አንድ ዩኒቨርስቲ በተጠቆምከው አቅጣጫ አሥር ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ ቦታ ሳይጠፋ የመንቀሳቀስ «እድልን» ያጎናፅፉሃል፤ እዚያ ከሰዎቹ ፊት ውጭ በቁጠባ ማህበራት እንደተሰጣቸው መንደር ሁሉም ያው ነው። ይህ የውስጥ ኪነ-ህንጻ መመሳሰል የሚነግረን ነገር ከምናየው ባለፈ የተዋቅሮአዊ መመሳሰልን ጭምር ነው ማለት ይቻል ይሆን!?፡፡ ይህ በከፍተኛ ትምህርት ውስጥ የሚጠበቀውን ‹‹የተለየ የማሰላሰያ ከባቢ›› በተለያየ ደረጃ መጫኑ አይቀርም፡፡ መግቢያው ደጃቸው ጋር ያለው የራስን ድባብ ይዞ የመለየት ሁኔታ ወደ ውስጥ ካልገባ ነገሩን ፍሬ አልባ ያደርገዋል፡፡ ወደ ውስጥ ማስገቢያውን በአጭሩ እንይና እናብቃ፡፡
በአንድ ካሪኩለም [ስርኣተ-ትምህርት] የቆረቡና የትምህርት ነጻነት እጦት የሚያንገላታቸው “Fit for purpose” ፈከርን Purpose ተደናግሮን በፊት ብቻ ቀረን ውድ አንባቢያን! ይህ ከላይ የምታነቡት ቁዘማ ነው፤ purpose ግብ ነው፡፡ … ሂደታችን እና አካሄዳችን መልክ የሚይዙት ከግባችን አንፃር ነው። ግብን ማወቅ እና መወጠን ደግሞ ጥሞናን ይሻል፤ ምንም እንኳን በአገራችን ያሉት የከፍተኛ ትምህርት
ተቋማት የመንግስት ቢሆኑም ፤ በሶስቱ የመንግስት ቅርንጫፎች እንዳሉት ተቋማት እንደ አንዱ መታየት ግን አለባቸው ወይ? የሚለው ጥያቄ መወያያ መሆን የሚኖርበት ይመስለኛል፡፡ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በአገራችን ካሉ ተቋማት ሁሉ ተለይተው አንድ የተለየ ነጻነት ይሰጣቸዋል (ማለትም ‹‹የትምህርት/የህሊና ነጻነት›› ) ። ይህ ነጻነት በጥንቃቄ የሚጠቀሙት ኻላል ጽንሰ ሃሳብ መሆኑ አሌ የማይባል ነው። አንጋፋው፣ የሃገራችን የሁለገብ እውቀት ባለቤት የሆኑት ፕሮፌሰር መስፍን «ዩኒቨርሲቲ ምንድን ነው?›› በሚል ርእስ [ከግማሽ ምዕተዓመት በላይ ባሰቆጠረ] በአንድ ወቅት በጻፉት ጽሁፋቸው ውስጥ ስለ የትምህርት ወይም የህሊና ነጻነት የሚከተለው ሰፍሮ እናገኛለን፦ በዩኒቨርሲቲ ማንም ሰው በአካላዊ ኃይል ወይም በጡንቻ እንዲጠቀም የማይፈቅድበት፣ ሰው ሁሉ በአስተሳሰብ በሕግና በማስረጃ ብርታት የሚመራበት፣ በሥራው ውጤትና ጥራት የሚመዘንበትና የሚከበርበት፣ ሁሉም ሥራዬ ብሎ እውነትንና ፍትሕን የሚከታተልበት ዓለም ነው፡፡ በዩኒቨርሲቲ ውስጥ ፍርሃትና ይሉኝታ ሥፍራ የላቸውም፡ ፡ የማይጠረጠርና የማይጠየቅም ነገር የለም፡ ፡ ለጊዜው መልስ የማይገኝ መስሎ ቢታይም የማይጠየቀውን ለመጠየቅ፣ የማይጠረጠረውን ለመጠርጠር ደፋር አእምሮና ንጹህ ኀሊና ያሻል፡፡ዩኒቨርሲቲ ልዩ ዓለም ነው፡ ፡ እያንዳንዱ የዩኒቨርሲቲ አባል የተጣለበትን አደራ የሚፈጽመው ያለበትን ኃላፊነትና ግዴታ በመረዳት ነው እንጂ በተወሰነ የሥራ ሰዓት ቁጥጥር ውስጥ በመሆንና በበላይ ባለሥልጣን ፍራቻ አይደለም፡፡ በዩኒቨርሲቲ ውስጥ ባለሥልጣን ማለት ለጥበብ፣ ለእውቀት፣ ለእውነት፣ ለፍትሕ ማስረጃን የጨበጠ፣ በአእምሮው ኃይልና በኀሊናው ንጽሕና ጓደኞቹ ክብርን ያጐናጸፉት ነው፡፡ አእምሮና ኀሊና
Vol. 3
ፍልስምና
በትእዛዝ ይደርቃሉ እንጂ አይለመልሙም፡፡ በዩኒቨርሲቲ ዓለም ውስጥ ፍርሃት የአእምሮ ድርቀት ምክንያት ነው፡፡ በዩኒቨርሲቲ ውስጥ ሰው ሁሉ ከፍርሃት ነፃ ሆኖ አእምሮው ያሳሰበውንና ኀሊናው ያመዛዘነውን ለመናገር፣ ለመጻፍና ለማሳተም መቻል አለበት፡፡ አእምሮ እንዲበለጽግ፣ እውቀት እንዲስፋፋ፣ ጥበብ እንዲያፈራ፣ አንዱ ትውልድ በሌላው ትውልድ እየተሻሻለና እየታደሰ እንዲሄድ ለሚፈልግ ሕዝብና መንግሥት ልዩ የአእምሮ ነፃነት ያላቸው ሰዎች በግድ ያስፈልጉታል፡፡ አእምሮ በፍርሃት ከታፈነና ኀሊና በጥቅም ከተሸጠ ዩኒቨርሲቲ የሚባለው መንፈሱን፣ ነፍሱን፣ ሕይወቱን እንዳጣ በድን የሚቆጠር ነው፡፡ የኔ ጥያቄ፣ የዚህ ነጻነት መንፈስ በዩኒቨርሲቲዎቻችን በር ላይ አልቆመ/ አልተንጸባረቀ እንደሆነስ ነው? ፣ በኪነህንጻው ላይ የሰፈረው የአንድ-አይነትነት መንፈስ በስርዓተ-ትምህርት [ኳሪኩለም] ላይም በብዛት ይታያል ፤ አንድ አይነት ይዘት ፣ አንድ አይነት የትምህርት አሰጣጥ ፣ አንድ አይነት አመዛዘን ፣ የምርቃት መዝሙሩ ሳይቀር አንድ አይነት! የዚህ ወጥነት መንስኤ ምናልባት ደግሞ ተቋማቱ፣ ግብ (purpose) አመንጪ መሆን ሲገባቸው ወደ ግብ አስፈጻሚነት ለመቀየር የሚሻ ፍላጎት ስለሚያንፀባርቁ እንደሆነ ፍንጭ ይሰጣል፡፡ ከዚያ ደግሞ የተቋማቱ ሙሉ ነጻነትን የመፈለግ ነገርም የማይተው ምክንያት ነው፡፡ አንዲት ቀለል ያለች ነገር አንስቼ ወጌን እቋጭ ዘንድ ወደድሁ፡፡
20 ነሐሴ 2012
amPhi
እንደተለመደው በአገራችን ባሉ የትምህርት ተቋማት ሁሉ ከመመረቂያ ገዋን ጋር የሚሰጠው ቆብ ከላዩ ዝርግ/ጠፍጣፋ ነው ፤ ይሁን እንበል፤ ግና የዚህ ጥፍጥፍ መደብ ተምሳሌትነቱ ከታላቁ ሳይንቲስት ኒኮላስ ኮፐርኒከስ በፊት ለነበረው የምድርን ጠፍጣፋነት ለሚያራምደው ሳይንሳዊ መላምት ወይም ‹ሀይፖተሲስ› ነው፡፡ ከመጀመሪያ ደረጃ ጀምሮ እስከ የከፍተኛ ትምህርት ድረስ በሚሰጡ ትምህርቶች የምድርን ሞላላነት ስናቀነቅን እንቆይና መደምደሚያችን ላይ ግን ጠፍጣፋዋን ምድር በመመረቂያ ቆባችን ጭነን እንወጣለን፤ ይህ የሚሆነው ላዩ ሞለል ያለ የመመረቂያ ቆብ አጥተን ነው? ወይስ በመንግሥት መመሪያ ታግደን ይሆን? ከዚህ ጀምረን ከላይ የተጠቀሰውን ሃሳብ እናስበው፤ ማሰብ ጥሪ ነውና፡፡ እንግዲህ በጎ አይጠበቅም፤ በጎው ነገር በበጎ ሃሳብ ውስጥ ይኖር ዘንድ ግድ ብሎታልና! በክፍል ሶስት ጽሁፌ፣ በአንድ ዩኒቨርሲቲ በነበረኝ ቆይታዬ ትዝብቴንና ልምዴን ለማካፈል እሞክራለው። እስከዚያው፣ የከርሞ ሰው ይበለን። አካላችን ይራራቅ፤ ሃሳባችን ግን ይቀራረብ፣ ይፋተግም፤ አዲሲቱ ሃሳብ ትወለድ ዘንድ!!! (በቃሉ ዋቺሶ በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ መምህር እና ተመራማሪ)
Vol. 3
ፍልስምና
amPhi
ዐይን የሌለው እንጀራና ሌሎች ክቦች ማርቆስ ዘመንበረ ልዑል
መተሳሰር ከምናየው የዘለቀ ስለመሆኑ ብዙዎቻችን እንስታለን። በጣልነው መጠን መውደቅ፥ ባነሳነው መጠን ከፍ ማለት እንዳለ... ህያው መሆናችን የእኛ ብቻ አበርክቶ ይመስለናል። ለመተንፈስ ስለወሰንሁ ብቻ እንደምኖር የሚሰማኝ ዕለት አለ። መንገዳችንን ስለማንቃኝ እኛ ብቻ ተራማጅ እንደሆንንም ይሰማን ይሆናል። ከተጓዘበት በላይ ጎዳናን ማን ያውቀዋል? ይሄ ክብ መመላለስ የእኔ እና አንቺ ጎዳና ነው። ይህ የመኖርን ጠልሰም የመሰለ፥ መነሻው የማይለይ፥ መሄጃው ከመምጫው የገጠመ መንገድ የእኛ ነው። ይህን ጎዳና ከመጓዝ ብዛት አውቀዋለሁ። ጎዳናው ራሱን ከሚያውቀው በላይ... በእንቅፋት የወለቁ ጥፍሮቼ፥የሌሎችም ጥፍሮች እና እንቅፋቱን ታክከው የወረዱ የደም ጠብታዎች የአፈሩ እርጥበት ውስጥ አሉ። አላፊ አግዳሚ ሃሳቦቻችን ሩቅ ምሥራቅ ከርመው የሚመለሱት በዚህ ጎርበጥባጣ መንገድ ነው። የዘነጋናቸውን፥ ቸል ያልናቸውን፥ ታይተው የጠፉንን ህልምና ሃሳብ መንገዱ ዳር ካለው ቱቦ ጠርዝ ላይ አልጌ ሠርተው ወይም እልፍ እያሉ በየሰው አጥር ከበቀለ ሐረግ ጤዛ ሁነው አልያም ጠጠሩን ገልበጥ አድርገን ብናይ ከአፈሩ ጋር ተነስንሰው አናጣቸውም። ይህ ጎዳና መኖራችንን ነው። እኛ ይህንን ጎዳና ነን። ይህ ጎዳና እኛን ነው! -------------------------------------
21 ነሐሴ 2012
የወጣሁት ከክብ ጋር ከተቆራኘ ሕብረተሰብ ነው። ገበታዬ በዕድሜ እርከን ደረጃ የሚሠራ ክብ ነው። የመጠጫ ሽክናዬ ለማስቀመጥ እንኳን እስኪቸግር ከክብ የተጣመረ ነው። ጉርሻዬ ክብ ነው። ጉርሻዬን የሚቀበለው አፍ አከፋፈቱ እንደ ጉርሻው መጠን ሰፊ እና ጠባብ ክብ ነው። ጎጆዬ፥ምድጃዬ እና እንጀራዬ ክብ ነው። ክበብን ከቅድስና ጋር በሚያቆራኝ ክብ ማሕበረሰብ ውስጥ የተፈጠርሁ አንድ ነጥብ ነኝ። ክብ መቼ ይፈርሳል? ፊት ለፊቴ ከቀረበልኝ እንጀራ ጋር እየታገልሁ ነው። ጥሎብኝ ትኩስ እና ዐይኑ ተደራርቦ የተጨፈነ እንጀራ አይዋጥልኝም። የቀረበልኝ እንጀራ በየአስር ሣንቲም ርቀት ላይ ድፍን ድፍን ያሉ ልሙጥ ክቦች ያሉበት ከፊል አነባበሮ ቢጤ ነው። የእንጀራ ነጠብጣዊ ውበት የሚጠፋው እንዲህ ሲሆን ይመስለኛል። ቦታቸውን ስተው ከላይ ለመከመር የሚጣደፉ ነጥቦች መልካሙን ክፍተት ሲደፍኑት። ከራሳቸው አልፈው የሌሎችን ነጥብነት በልሙጥነት ሲቀይሩት። ወጥ እና መረቅ ካልዘለቀው እንጀራ እንጀራነቱ ስለሚቀር... ክብን ነጥብ ያፈርሰዋል። ሥርዓት በሌለው አነጣጠብ የትም ያረፈ ነጥብ። የሌላው ነጥብነት ለመንጠቅ ድርብ የተሳለ ነጥብ። ቦታቸው ሳይለቁ ጨረራቸው ወደአንድ መሐል ከሚጠቁም ነጥቦች መሐል የተዛነፈ መስመር ያሰመርሁ ነጥብ ነኝ። ዙሪያዬን ከከበበኝ ክብ ያለሥርዓት መሠለፌ ከእኔ አልፎ ክበቤን አፍርሶታል። ---------------------------
ስለመኖር.... መንገዴን እመስላለሁ። በአቧራው በምኑ ሳይሆን እንደአጀማመሬ መፈጸም ልማዴ ስለሆነ። ካለመኖር ዞሬ አለመኖር ላይ ስለማርፍ። ምንም ብዛነፍ አብሬ ባጠመምሁት ምኅዋር ውስጥ ሌላ ልሙጥ ክበብ ስለምዞር። የማናመልጠው ነገር አለ። ሞት! መኖርን የምንሸሸው ከመኖር ጫፍ ባክኖ መሞትን ስለምናስተውል ነው። የሞት ምርኮኞች ነን። ጎዳናዬ ከማይታየኝ ደቃቃ ነፍሳት እስከ ግዙፍ መላጣ ሰው ሞት አስተናግዷል። ጎዳናዬን የምመሰል እኔም የሞት ምርኮኛ፥ የሞት እድምተኛ ነኝ። መኖሬን እስከምስት፥ መቆሜን እስክጠራጠር በሞትና በውድቀት ተከብቤያለሁ። ------------------------------እዚች አሁኗ ቅጽበት ላይ ..... አንድ ሲኒ ቡና፥ ቆንጆ ወርቃማ ጀንበር፥ ከፍቼ የተውሁት መጽሐፍ፥ ነፋሱን የተወዳጀ ዝግ ያለ ሙዚቃ ያሉበት አሁን ላይ...... ክበቤን ስላፈረስሁት ነጥብ እና ዐይን ስለሌለው እንጀራ እያሰብሁ ተቀምጬ በሃሳብ እሞግታለሁ። ከልሙጡ ሥር እንጀራው ምን ያህል ተሳስሯል? ከማየው ዘልቆ ያለው ተጻምሮ ምንድነው? ከመዛነቄ የመጣ አዲስነት ለክበቤ ውበት ምን አበርክቷል? ..... ነጥብነቴ ጠማማ መስመር ቢሰራም ውድቀቶች መካከል መቆሜ፥ ሞት አፍንጫ ሥር ህያው መሆኔ ቁም ነገር ሆኖኝ ሃሳቤ ላይ እንሳፈፋለሁ። እላለሁ.....”ሁላችን የሞት እድሞተኞች ነን!” እናም እዚች አሁኗ ቅጽበት ላይ ..... አንድ ሲኒ ቡና፥ ቆንጆ ወርቃማ ጀንበር፥ ከፍቼ የተውሁት መጽሐፍ፥ ነፋሱን የተወዳጀ ዝግ ያለ ሙዚቃ ያሉበት አሁን ላይ...... የሚያወራኝን ጎዳና አንድ ነገር እጠይቃለሁ.... “Am I not living now?” “አሁን እየኖርሁ አይደለምን?”
Vol. 3
ሚስማር ተራ
amPhi
እኔ ምሞተው ዛሬ ማታ ትንሳኤ ዘርፉ (የሮማን ዘውዴ ልጅ)
`ኢትዮጲያን አዲስ የቁማር ጋኔል ለክፏታል!`--- ዘ ኢኮኖሚስት በባለፈው ፅሁፋችን በሃገራችን በከፍተኛ ሁኔታ የተንሰራፋውንና ነፋስ እንዳየው ሰደድ ሀገሪቱን ያቀጣጠለውን…ዛሬም ድረስ እልባት ያልተገኘለትን የስፖርታዊ ውርርድ(ቁማር) ጉዳይ አንስተን ከማባያ አንፅሮቶቹ እስከ ስነ-ልቦናዊ ጠገጎቹ ድረስ ዳሰሳ አድርገናል፡፡ ለዛሬ ደግሞ በሌሎች ሃገራት የተወሰዱ ህጋዊ እርምጃዎችን በመጠቃቀስ ሃገራችንም ልትጓዝ የምትችልባቸውን የመፍትሄ መንገዶች በጥቂቱ ለማመላከት ጥረት እናደርጋለን፡፡ በዓለም አቀፍ ደረጃ የ150 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር አመታዊ ኢንዱስትሪ የሆነው የስፖርት ቁማር ከውልደቱ አስንስቶ አሁን ያለበት ደረጃ እስኪደርስ እንደ አፍሪካ ያለ ተስማሚ ቦታን አግኝቶ የሚያውቅ አይመስልም፡፡ ከደበቡ አፍሪካ እስከ ናይጄሪያ፣ ከዩጋንዳ እስከ ታንዛኒያ፣ ከጋና እስከ ኬኒያ ቅርንጫፎቹን አጎልብቶ፣ስሩን ሰዶ አብቦ እና ጎምርቶ የተንሰራፋባቸው ሀገራት ናቸው፡ ፡ በዚህ ከነ ግሳንግስና ውጥንቅጡ ልናገባድድ በተቃረብነው አመት ደግሞ ሀገራችን ላይ ጆፌውን የጣለበት ነበር ማለት ይቻላል፡፡ የብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደርን እንደገና ለማቋቋም በወጣው አዋጅ ቁጥር 535/2007 ‹‹የስፖርት ውርርድ ሎተሪ ማለት በቤት ውስጥ ወይም ከቤት ውጪ የሚከናወኑ የስፖርት ውድድሮችን መሰረት በማድረግ የሚደረግና ሽልማቱ በገንዘብ ወይም በአይነት የሚሰጥ ሎተሪ ነው፡፡›› ይለዋል፡፡ ይህንንና ነገሩን በስፖርት ውርርድነት የሚደነግገውን አዋጅ ቁጥር 543/2007ን መሰረት አድርገው ነው እንግዲህ ቁማርና አቋማሪ ክረምት እንዳየ አሸን በአገሪቱ መፍላታቸው፡፡
22 ነሐሴ 2012
“ገንዘብ የምትታለብ ላም እንደማለት ነው”-ይሉታል የንግዱ ባለቤቶች፡፡ “ገንዘባችንን ለማስመለስ ነው የምንጫወተው” ---ተቋማሪዎቹ ባንፃሩ “በሬ ሆይ ሳሩን ብቻ አይተህ ገደሉን ሳታይ…” ሆነው፤ የህዝባቸውን ንቃተ ህሊና ባግባቡ ሳይገመግሙ ራሳቸውን በአዙሪቱ እንደተዘፈቁ ያገኙት ጎሮቤቶቻችን ጉዳዩ በትውልዳቸው ላይ ያደረሰውን የህሊና ልምሻ ከረፈደም ቢሆን ተገንዝበው ፈቃድ የሰጡበት የህግ ብትራቸውን መሰብሰብ ከጀመሩ ሰንበትበት አሉ፡፡ ዩጋንዳ- ለዚህ ተጠቃሽዋ ሀገር ነች፡፡ባሳለፍነው አመት አጋማሽ የሀገሪቱን ፕሬዝዳንት ትዕዛዝ ተከትሎ ሀገሪቱ ለአዳዲስ አቋማሪ ድርጅቶች ፈቃድ መስጠት ማቆሟንና ያሉትንም ቢሆን ፈቃድ እንደማታድስ አስታውቃ ነበር፡፡ “ቁማር የሀገሬን ወጣቶች ሀሳብ ከስራ አፋቷል” ይላሉ--ፕሬዝዳንቱ ዩሬ ሞሴኒ፡፡ “መንግስት ለነገሩ እልባት መስጠት አስፈልጎታል ምክኒያቱም የሀገራችን ዜጎች እንዲበለፅጉ የምንሻው በስራ እንጂ፤ ድንገት በሚመጣ እና ምንጩ በማያስተማምን ገቢ ላይ ተመስርተው እንዲሆን አይደለም” በማለት በቀጥታ ትዕዛዝ ፈቃድ መስጠቱን እንዲያቆም የሀገሪቱን የሎተሪ አስተዳደር አዝዘዋል፡፡ ለዚህ ውሳኔ ደግሞ የሃገሪቱ የሃይማኖት መሪዎች ያደረጉት ጫና ቀላል የሚባል አልነበረም፡፡ የሷን ፈለግ ለመከተል ከወር በላይ ጊዜ ያልፈጀባት ጎሮቤት ሀገር ኬኒያም በሀገር ውስጥ ሚኒስተሯ በኩል “የቁማር ኢንዱስትሪውን አብጠርጥሬ ፈትሻለሁ፤ ፈቃድ አሰጣጡንም በዓይነ-ቁራኛ እከታተላለሁ” ማለቷን የምናስታውሰው ነው፡፡
ታዲያ ከጎረቤቶቻችን ዘንድ የሚሰሙት እንደዚህ ያሉ ቆፍጠን ያሉ ህጋዊ እርምጃዎች የኛኑም ሀገር መሪዎች ለማንቃት ደወል ይሆናሉ ብለን ተስፋ እናደርጋለን፡፡ ቀድሞ ነገርም ቢሆን “የአበራሽን ጠባሳ ያየ በእሳት አይጫወትም” ብለው ያለመጠንቀቃቸው ነገር ቢያስተዛዝበንም ቅሉ… ከእኛም ዘንድ ቢሆንም ግን አስፈላጊው ህጋዊ መፍትሄ እንዲሰጥ ጫና በማሳደር በኩል ትልቅ ሃላፊነት ይጠብቀናል፡፡ የሚዲያ ተቋማት፣ ተፅዕኖ ፈጣሪ ሰዎች፣ የሃይማኖት ተቋማትና ሌሎችም በከፍተኛ ሁኔታ መንቀሳቀስ ይኖርባቸዋል፡፡ ነገሩን የአንድ ወቅት የማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ ከማድረግም በዘለለ ተቋማዊ እና ህጋዊ መፍትሄ እስኪገኝ ድረስ መታገልም ግድ ይላል፡፡ በመንግስት በኩልም የአልኮል መጠጦችና ትምባሆ ምርቶችን ዜጎች በስፋት እንዳይጠቀሙ ማስታወቂያዎችን እስከ መከልከል የተሄደበት ርቀት በዚህም ዙሪያ ሊደገም ያስፈልጋል፡፡ በርግጥ የሎተሪ አስተዳደሩ በወርሃ ጥር ለአዳዲስ አቋማሪዎች ፈቃድ መስጠት ማቆሙን ቢገልፀም ከዛ ቀጥሎ ባሉት 6 ወራት ግን ከዚህ የዘለለ ምንም እርምጃ ሲወስድ አላየንም፡ ፡ በተናጠል በአማካይ ከ30 በላይ ቅርንጫፎች ያሏቸው 22 አቋማሪ ድርጅቶችም ንግዳቸውን ሲያስፋፉ እንጂ ሌላ የተሻለ ነገር ሲሆን አልተመከትንም፡፡ይባስ ብሎም ባንኮቻችንም ሳይቀር የኢንተርኔት አገልግሎቶቻቸውን ከነዚህ ተቋማት ጋር በማስተሳሰር ከቤታችሁ ሳትወጡ በተቀመጣችሁበት ሆናችሁ ተቋመሩ እያሉን ነው፡ ፡ የህብረተሰብ አገልግሎት መስጠት ከማህበራዊ ኃላፊነት ጋር የሚመጣ መሆኑን ጨርሰው የዘነጉት ይመስላሉ፡፡
Vol. 3
ሚስማር ተራ
የሃገራችን ህግ ቁማርን እድሜያቸው ከ18 አመት በላይ ለሆኑ ብቻ ቢፈቅድም አብዝሃኛዎቹ ደምበኞቻቸው የሁለተኛ ደረጃ ት/ትን እንኳን ባግባቡ ያላጠናቀቁ አፍላዎች እንደሆኑ ራሳቸው አቋማሪዎቹም ሳይቀር የሚመሰክሩት ሃቅ ነው፡፡ ለስፖርትና ማህበራዊ ተቋማት ይሰጣሉ የተባለውን ድጋፍም ቢሆን ማንም ህጋዊ ነኝ የሚል አካል ጠይቋቸው እንደማያውቅ ነው የሚናገሩት፡፡ እዚህ ላይ ልብ ማለት ያለብን ነገር ግን ሀገራችን ፈፅሞ የስፖርታዊ ውርርዱን መፍቀድ የለባትም የሚል ግትር አቋም መያዙም የማይበጅን መሆኑን ነው፡፡ ይልቁንስ የንግድ ድርጅቶቹን ሀገር በቀል እንዲሆኑ ከማድረግ ጀምሮ ሌሎች ከልካይ እቀባዎችን በማድረግ ትኩሳቱን የማለዘብ ስራ መሰራት ይኖርበታል፡፡ ለዚህ ደግሞ ቅደም ብለን ካነሳናት ሀገር-ዩጋንዳ የተሻለ ጥሩ ምሳሌ አናገኝም፡፡ የነገሩን ጉዳት አምጪ ባህሪያት ሊገድቡ የሚችሉ ክልከላዎችን ጥሩ አድርጋ በህጓ ውስጥ አካታለች፡፡ ከነዚህም መካከል ለመጠቃቀስ ያህል ክልከላ
-የአሳሳች የቁማር ማስታወቂያዎች
(በማስታወቂያዎች ላይ ተገቢ ያልሆኑ ገለፃዎችን የሚከለክል ሲሆን በሁሉም ማስታወቂያዎች ላይ በየማቋመሪያ ቤቱ፣ በመቋመሪያ ማሽኖች እና በይነ-መረቦች ላይ “ቁማር ሱስ አምጪ ነገር ነው፡፡የስነ-ልቦና ጉዳትም ሊያደርስ ይችላል!” የሚል ማስጠንቀቂያን እንዲለጥፉ ማስገደድንም ይጨምራል፡፡) -ከእድሜ በታች የሆኑ ተቋማሪዎችን (ህፃናትን) ክልከላ (ይህም እያንዳንዱ አቋማሪ አገልግሎት ከመስጠቱ በፊት ማንነትን የሚገልፅ መታወቂያ
23 ነሐሴ 2012
መጠየቅን ያስገድዳል) -የቁማር ቤቶች የአገልግሎት ሰዓት ገደብንና -በት/ት ቤቶችና ሌሎች የት/ት ተቋማት የቁማር ድርጊትን መከልከልን ያካትታል፡፡ (Statutory instruments supplement, the Uganda Gazette No.4, volume CX, dated 20th Jan 2017) ከሶስት አመታት ያልዘለለ እድሜ በሃገራችን ያለው ኢንዱስትሪው መቀዛቀዝ ዳጎስ ያለ ትርፍን መንግስትን ቢያሳጣውም በአስር ቢሊዮኖች ከምትከስረው ዩጋንዳ ጋር ሲነፃፀር ግን ጊዜው አልረፈደብንም ያስብላል፡፡ ህግን ማውጣት ብቻ ሳይሆን የአፈፃፀም ሂደቶቹን መንደፍም እርጋታንና ጥናትን የሚጠይቅ ጉዳይ መሆኑ እሙን ነው፡፡ አቋማሪ ተቋማቱን እንደልብ እንዲሰሩ ፈቅዶ -ጉዳቱ እየደረሰ ባለበት ሁኔታ ጥናት አካሂዳለሁ ማለት ግን፡ “እኔ ምሞተው ዛሬ ማታ፣ ላሜ ‘ምትወልደው ለፍልሰታ” አይነት ፈሊጥ ላይ እንዳይጥለን ፈራለሁ፡፡ በቸር ያቆየን (ትንሳኤ ዘርፉ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ)
amPhi
Vol. 3
ጋሜ
amPhi
ሞዴሊንግ ስንል... ሙሴ ካሳሁን
ሰላም የአምፊ መፅሔት ተከታታዮች ባለፈው ስለ ኢትዮ ፋሽን ከኔ ጋር ቆይታ አድርገን ነበር፡፡ ከዛም ብዙዎች አበረታትታችሁኛል አስተያየትም ሰጥታችሁኛል በጣም አመሰግናለው፡፡ ዛሬ ደግሞ ስለሞዴሊንግ አንዳንድ ነገሮች ልላችሁ ተገኝቻለሁ አብራችሁኝ ቆዩ፡፡ ሞዴሊንግ የፋሽን አንድ አካል ሲሆን እና በውስጡ ብዙ ዘርፎች ያሉት ትልቅ ሙያ ነው፡፡ሞዴል ማለት የአንድ ነገር መገለጫ ተምሳሌት ወይም ማሳያ ልንለው እንችላለን፡፡ ሞዴልነት በሰውነት አካሎች የመናገር ጥበብ ነው፡ ፡ አንድ ሰው ለአንድ ተቋም ተቀጥሮ ለምርቶቻቸው ማሳያ ከሆነ እና ለማስታወቂያነት የሚውል ከሆነ ያ ሰው ሞዴል ሆኖ ሰርቷል ማለት እንችላለን፡፡ ከላይ ልጠቅሰው እንደሞከርኩት ሞዴሊንግ ዘርፈ ብዙ ነው፡፡ ከነዚህ የተወሰኑትን እንመልከት… 1.የመድረክ (Run way) ሞዴል እነዚህ ሞዴሎች በመድረክ ላይ በዲዛይኖቻቸው የተዘጋጁ አልባሳትን ለብሰው ለተጠቃሚዎች የሚያሳዩ ናቸው፡፡ እነዚህ ሞዴሎች በአለምአቀፍ መስፈርት ከ1.83ሜ በላይ ሴቶች ከ1.75ሜ በላይ እና የተስተካከለ አቋም የሚፈልግ ነው፡፡ 2.ፋሽን (Fashion, editorial)
ሞዴል እነዚህ ሞዴሎች የሚታዩት በትልቅ የፋሽን ሾው መጽሔቶች ላይ ነው፡፡ የሚሰሩላቸው ድርጅቶችም እውቅናን ያተረፉ ትልቅ ድርጅቶች ናቸው፡፡ ለምሳሌ Gucci, Prada, Marc Jacops, Versace እና የመሳሰሉት ናቸው፡፡ እናም እነዚህ ሞዴሎች የተመረጡና ትልቅ ደረጃ ላይ የሚገኙ ናቸው፡፡አቋማቸው ደግሞ ረጅም፣ ቀጭን ሲሆኑ ባጠቃላይ ‹‹ complete package ›› ሚባሉት ናቸው፡፡ 3.የመዋኛ እና የውስጥ ልብስ ሞዴል እነዚህ ሞዴሎች የዋና ልብሶችና የውስጥ ልብሶች የሚያስተዋውቁ ሞዴሎች ናቸው፡፡ እነዚህ ሰዎች በራስ መተማመናቸውና ስነ-ልቦናቸው ከፍ ያለ ነው፡፡
24 ነሐሴ 2012
4.የንግድ (commercial ) ሞዴል እነዚህ ሞዴሎች በእድሜ፣ በቁመትና በመጠን ያልተገደቡ ናቸው፡፡ ማንኛውም ተሰጦ ያለው ሰው ሊሳተፈበት የሚችል ዘርፍ ነው፡፡ 5.የአካል ብቃት(Fitness) ሞዴል እነዚህ ሞዴሎች አቋማቸው በደንብ የዳበረ እና ያማረ ሞዴሎች ናቸው፡፡ እነዚህ የሚሰሩትም ልዩ የሆኑ ስራዎች አቋም የሚፈልጉ፣ ያሸበረቁ ልብሶችና ማስታወቂያዎች ላይ ነው፡፡ ብዙ ጊዜ እነዚህን ሰዎች በንግድ ሞዴል ውስጥ እናገኛቸዋለን፡፡ 6.Parts ሞዴል እነዚህ ሞዴሎች ከሰውነት ክፍላቸው ለየት ያለና የሚስብ ያካል ክፍላቸውን በማስታወቂያ የምንጠቀምበት ዘርፍ ነው፡፡ለምሳሌ እጃቸውን ለጌጣጌጥ እግራቸውን ለጫማዎች እና የተለያዩ የውበት መጠበቂያ መሳሪያዎቸን የምናስተዋውቅበት ዘርፍ ነው፡፡ 7. የማስታወቂያ(Promotional) ሞዴል ይህ የሞዴል አይነት ተጠቃሚዎች ያሉበት ስፍራ ላይ በመገኘት ስራውን በደንብ እያስተዋወቁ የማሻሻጥ ስራውንም የሚሰራ ነው፡፡በዚህ ጊዜ ይህ ሞዴል ከሌሎች ለየት የሚያደርገው የግል ሂውቱ በገበያወ ላይ ተጽእኖ መኖሩና ስለሚሰተዋወቀው ነገር በቂ አውቀተና መረጃ መኖሩ ነው፡፡ 8.የፊት ቅርጽ (Glamour) ሞዴል ይህ የሞዴል ዘርፍ የፊት ውበትና ቅርጽ ላይ ያተኮረ ነው፡፡ 9.የህትመት (Print) ሞዴል እነዚህ ሞዴሎች የሚግኙት በመጽሔት billboard company booklets flairs
እና posters ላይ ነው እነዚህን ሞዴሎች ንጹህ ቆዳና ማራኪ ፈገግታ ያላችው ናቸው፡፡ ዛሬ ላይ በሀገራችን በርካታ የሞዴሊንግ ትምህርት ቤቶች ተከፍተዋል በዚህም ምክንያት በርካታ ሞዴሎች በኢትዮጵያ ውስጥ ይገኛሉ፡፡ ነገር ግን ይህ የቁጥር መብዛት በሰዎች ላይ ስለ ሞዴሊነግ ዝቅተኛ አመለካከት እየጫረ ይገኛል ሆኖም ሁላችሁም እንድትረዱት የምፈልገው ነገር የሞዴሊንግ ሰርተፊኬት የያዘ ሁሉ ሞዴል አይደለም ይህ እኔ እና ጓደኞቼንም ይመለከታል። ሞዴል አይደለንም ግን መንገዱን ጀምረናል፡፡ ሞዴልነት ተምሳልት ነው ካልን፤ ስንቶቻችን ለወጣንበት ማህበረሰብ ምሳሌ የሆነው? መቼ ነው ድምጽ የሆነው? የማህበረሰቡን ችግር ተረድተናል ወይ? የሚለውን ጥያቄ መመለስ አለብን፡፡ አንድ ሰው ሞዴል ሆነ የምለው በእናንተ ስኬት ውስጥ ሌሎች ራሳቸውን ማየት ሲጀምሩ ነው። ራሳችንን ሳናስተዋውቅ ስራዎቹ ስለኛ መናገር ሲጀምሩ ነው፡፡ ለኔ ሞዴልነት ያ ነው፡፡ ስለዚህ ራሳችንን አሁን ሞዴል እንዳልሆንን ነገር-ግን መሆን እንደምንችልና እንደምናሳካው አምነን ራሳችንን እዛ ትግል ውስጥ መክተት አለብን፡ ፡ ሞዴል ለመሆን በምናደርገው ትግል ውስጥ ትልቅ ዲዛይነር ለመሆን በምናደርገው ትግል ውስጥ ትልቅ ንቅናቄ በፋሽን ኢንደስትሪው ላይ እንፈጥራለን ብዬ አስባለው፡፡ ስኬት ደግሞ የስራ የልፋት ውጤት ነው፡፡ ሰርተፊኬትና ፎቶዎች ስላሉን ሞዴል ሆንን ብለን ልንዘናጋ አይገባም፡፡ እሱ የተሳሳተ ፍቺ ነው፡፡ ለዚህ ደግሞ የሞዴሊንግ ትምህርት ቤቶች ትልቁን ሃላፊነት መውሰድ አለባቹ፡፡ ተማሪዎች ይዘው የመጡትን አላማ እንዳይረሱ ማድረግ የናንተ ሃላፊንት ነው፡ ፡ ዛሬ ሁላችንም ትልቅ ሞዴል ለመሆን እንስራ፡ ፡ ስንጀምር የያዝነውን አላማና ወኔ እናስታውስ፡፡ ትልቅ የማንሆንበት ምክኒያት ምንም የለም፡፡ አመሰግናለሁ
(ሙሴ ካሳሁን, የዩኒቲ ዪኒቨርሲቲ ተማሪ
እና የአ.ሳ.ቴ.ዩ ኮምፒውተር ሳይንስ እና ምህንድስና ተማሪ)
Vol. 3
አመልካች ጣት
amPhi
Ethio Art &Arc
ሄላ ከድር
የማህበራዊ ድረ-ገጾችን ለፈለግነዉ አላማ መጠቀም እንችላለን:: እሱን መብታቸውን ተጠቅመው ብዙዎች ብዙ ሲያረጉ አይተናል፤ ነገር ግን ከዚህ ሁሉ መሀል ለጥሩ ዓላማ ተነስቶ የሚበረታታ ስራ የሰራ ላይ Ethio Art & Arc የተባለ የቴሌግራም ቻናል ለማስተዋወቅም ወደድኩ :: የኪነ-ህንፃ(Architecture ) ተማሪዎች በየሴሚስተሩ የሚሠሯቸው ፕሮጀክቶች ከአስተማሪ ግምገማ እና ሴሚስተር ውጤት በኋላ የጁሪ (jury presentation) ወረቀት ከመጣል ዋናው ሰነድም (source file) የኮምፒውተር ክምችት ከማጣበብ የዘለለ ብዙም ጥቅም የለውም። ብዙ ጊዜ ይህ ነገር ተማሪዎችን የፈተና ነጥብ ተኮር ስራ እንዲሰሩ ከማድረጉ በላይ በሞራል ከመጀመሪያው የተሻለ ሥራ እንዳይሰሩ ያደርጋል። ይህ ያሳሰባቸው ሁለት የአዳማ ሳይንስ እና የቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ 4ኛ ዓመት የኪነ-ሕንጻ (Architecture) ተማሪዎች ብዙም ባይሆን ትንሽ ማበረታቻ ትሆናቸው ዘንድ ፕሮጀክቶቹን አወዳድሮ ለመሸለም በዋናነት ደግሞ የ ተማሪዎቹን ችሎታ አውጥቶ ለማስተዋወቅ በማሰብ ቻናሉ የከፈተ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት በኪነ-ሕንጻ (Architecture) ተማሪዎች በተጨማሪ የጥበብ ስራዎች ላይ ተስጥኦ እና ፍላጎት ያላቸውን ወጣቶች በሙያው ላይ ትልቅ ቦታ በደረሱ ዳኞች አወዳድሮ የሚሸልም እንዲሁም ተስጦአቸውን እንዲያወጡ በማበረታታት ከሰው ጋር የሚያስተዋውቅ ቻናል ነዉ :: በዚህ አድራሻ በቴሌግራም ቤተሰብ ሁኑን @ newlifearts @newlifearts (ሄላ ከድር፣ የአ.ሳ.ቴ.ዩ ኪነ-ሕንጻ ተማሪ)
25 ነሐሴ 2012